እውነተኛ ፡ ዳኛ (Ewnetegna Dagna) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 4:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የክሱን ፡ ክምችት ፡ የዕዳውን ፡ ጽህፈት
ደምስሰህልናል ፡ በመስቀልህ ፡ ምህረት
አንተ ፡ አጽድቀኸናል ፡ ማነው ፡ የሚከሰን
ከጸናችው ፡ እጅህ ፡ የለም ፡ የሚነጥቀን
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ተመሥገን

አዝ፦ አንተ ፡ የእውነት ፡ አምላክ ፡ እውነተኛ ፡ ዳኛ
ከከሳሽ ፡ ያዳንከን ፡ ፈርደህልን ፡ ለእኛ
ጌታ ፡ ከመንበርህ ፡ ከጽድቅ ፡ ዙፋንህ
መድኃኒትን ፡ ልከህ ፡ በአንተ ፡ አርፏል ፡ ሕዝብህ

ተረታሁኝ ፡ ብሎ ፡ ጠላትም ፡ ባይተኛ
የማንተቀላፋ ፡ ጌታ ፡ አለህ ፡ ለእኛ
ደምፅህን ፡ ሲሰማ ፡ አጥማጅህ ፡ ገለል ፡ ይላል
ከመከራም ፡ ስጋት ፡ በአንተ ፡ ያመነ ፡ ያርፋል
ተከልሎ ፡ ይኖራል

አዝ፦ አንተ ፡ የእውነት ፡ አምላክ ፡ እውነተኛ ፡ ዳኛ
ከከሳሽ ፡ ያዳንከን ፡ ፈርደህልን ፡ ለእኛ
ጌታ ፡ ከመንበርህ ፡ ከጽድቅ ፡ ዙፋንህ
መድኃኒትን ፡ ልከህ ፡ በአንተ ፡ አርፏል ፡ ሕዝብህ

ከሳሻችን ፡ ወድቆ ፡ እኛ ፡ ተነስተናል
ጉልበታችን ፡ ፀንቶ ፡ እነሆ ፡ ቆመናል
ታዳጊያችን ፡ ሆይ ፡ ተመሥገን ፡ እንበልህ
ከአዳኙ ፡ ወጥመድ ፡ የወጣን ፡ ሕዝበህ
ማርኮናል ፡ ፍቅርህ

አዝ፦ አንተ ፡ የእውነት ፡ አምላክ ፡ እውነተኛ ፡ ዳኛ
ከከሳሽ ፡ ያዳንከን ፡ ፈርደህልን ፡ ለእኛ
ጌታ ፡ ከመንበርህ ፡ ከጽድቅ ፡ ዙፋንህ
መድኃኒትን ፡ ልከህ ፡ በአንተ ፡ አርፏል ፡ ሕዝብህ