አዎን ፡ ይሆናል (Awon Yehonal) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 6:26
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በጌተ ፡ ሰማኒ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ቃቶ
በቀራንዮ ፡ ላይ ፡ ከጠላት ፡ ተዋግቶ
በጐቹን ፡ አድኗል ፡ ነፍሱን ፡ ለሞት ፡ ሰጥቶ
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ፍቅር ፡ ከየት ፡ ይገኛል ፡ ከቶ (፫x)

መልካም ፡ እረኛ ፡ ስለ ፡ በጐቹ
ነፍሱን ፡ ያኖራል ፡ በእርሱ ፡ የሚገባ
በእርሱም ፡ የሚሰማራ ፡ ለዘለዓለም ፡ ይድናል
ዘለዓለም ፡ ይኖራል

መንጋውን ፡ ሊበትን ፡ እረኛውን ፡ መቶ
ሰይጣን ፡ ቢጣጣርም ፡ እጅግ ፡ ተበራቶ
ምርኮውንም ፡ መልሷል ፡ ኢየሱስ ፡ ድል ፡ ነስቶ
ዛሬም ፡ ይደግመዋል ፡ ሕዝቦቹን ፡ ጐብኝቶ (፫x)

አዎን ፡ ይሆናል ፡ መቼ ፡ ይቀራል
እንጠብቃለን ፡ ለቅሷችንን ፡ በደስታ
ኢየሱስ ፡ ለውጦልን ፡ ብርሃንን ፡ እናያለን (፪x)

ሃዘንተኞች ፡ ስንሆን ፡ ዘወትር ፡ ደስ ፡ ይለናል
ዓለም ፡ የሌላትን ፡ መድህን ፡ አግኝተናል
ስለዚህም ፡ እኛ ፡ ምንም ፡ ብንገፋ
ማንም ፡ አይጥለንም ፡ ከዚህ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋ (፫x)

አዎን ፡ ይሆናል ፡ መቼ ፡ ይቀራል
እንጠብቃለን ፡ ለቅሷችንን ፡ በደስታ
ኢየሱስ ፡ ለውጦልን ፡ ብርሃንን ፡ እናያለን (፪x)

በቅርብ ፡ በሩቅ ፡ የተበተናችሁ
ጌታ ፡ ቅርብ ፡ ነውና ፡ ፍፁም ፡ አይክፋችሁ
የእርሱን ፡ በጐነት ፡ ለዓለም ፡ ተናግራችሁ
ለጽዮን ፡ ስብሰባ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ያብቃችሁ (፫x)

ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ቶሎ ፡ ቶሎ ፡ ና
ናና ፡ ሰብስበን ፡ ከተበታተንበት
ወደ ፡ ውድ ፡ አገራችን ፡ ጥራን ፡ አከማቸን (፪x)

አዎን ፡ ይሆናል ፡ መቼ ፡ ይቀራል
እንጠብቃለም ፡ ለቅሷችንን ፡ በደስታ
ኢየሱስ ፡ ለውጦልን ፡ ብርሃንን ፡ እናያለን (፪x)

አዎን ፡ ይሆናል ፡ (አዎን ፡ ይሆናል)
መቼ ፡ ይቀራል ፡ (መቼ ፡ ይቀራል)
እንጠብቃለን ፡ ለቅሷችንን ፡ በደስታ
ኢየሱስ ፡ ለውጦልን ፡ ብርሃንን ፡ እናያለን (፪x)