ጠቢብ ፡ በጥበቡ ፡ አይመካ (Tebib Betebebu Aymeka) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 3:09
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አመጻዬ ፡ ወደ ፡ ምድረ ፡ በዳ ፡ ወሰደችኝ
ውኃ ፡ በሌለው ፡ በረሃ ፡ አንከራተተችኝ
ለውድቀቴ ፡ እውቀት ፡ ትዕቢትን ፡ አስተማረችኝ
ጥማት ፡ ሲያቃጥለኝ ፣ እልህ ፡ ሲታገለኝ
እውነት ፡ ስትወርሰኝ ፣ ጥበብ ፡ ስትገስጸኝ
መንፈሱ ፡ ሲረታኝ ፣ ጌታን ፡ አገነሁት

አዝ፦ ጠቢብ ፡ በጥበቡ ፡ አይመካ
ኃያልም ፡ በኃይሉ ፡ አይመካ
ሁሉን ፡ ቻይ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጽድቅንና ፡ ፍርድን
በምድር ፡ ላይ ፡ ማድረጉን ፡ ያወቀ
በጌታ ፡ ይመካ (፪x)

ሰማያዊ ፡ ጥበብ ፡ ዓይንን ፡ ትከፍታለች
ለሰነፎች ፡ ብልሃትን ፡ ታስተምራለች
ከምዝምዝ ፡ ወርቅና ፡ ከቀይ ፡ ዕንቁ ፡ ትበልጣለች
አጥብቀህ ፡ ብትሻት ፡ ብትፈላልጋት
ድምጽህን ፡ አንስተህ ፡ ጥበብን ፡ ብጠራት
ያን ፡ ጊዜ ፡ ታውቃለህ ፡ እግዚአብሔርን ፡ መፍራት

አዝ፦ ጠቢብ ፡ በጥበቡ ፡ አይመካ
ኃያልም ፡ በኃይሉ ፡ አይመካ
ሁሉን ፡ ቻይ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጽድቅንና ፡ ፍርድን
በምድር ፡ ላይ ፡ ማድረጉን ፡ ያወቀ
በጌታ ፡ ይመካ (፪x)

የዚህች ፡ ዓለም ፡ መርማሪ ፡ ወዴት ፡ አለ
የዘመናትን ፡ ጥያቄ ፡ ያቃለለ
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ሊቁ ፡ ለእኛ ፡ የተሰቀለ
ከበረሃው ፡ መሃል ፡ ሕይወት ፡ ያፈለቀ
የሰይጣንን ፡ ስልጣን ፡ መትቶ ፡ ያደቀቀ
ለእርሱ ፡ ስንሸነፍ ፡ ጥያቄው ፡ አለቀ

አዝ፦ ጠቢብ ፡ በጥበቡ ፡ አይመካ
ኃያልም ፡ በኃይሉ ፡ አይመካ
ሁሉን ፡ ቻይ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጽድቅንና ፡ ፍርድን
በምድር ፡ ላይ ፡ ማድረጉን ፡ ያወቀ
በጌታ ፡ ይመካ (፪x)