ከንስሃ ፡ ወዲያ (Keneseha Wedya) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 3:08
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የጠላትህን ፡ ክስ ፡ ሊደመስስልህ
ከዓብ ፡ ዘንድ ፡ የቆመ ፡ ጠበቃ ፡ አለልህ
የኃጢአትህን ፡ ሸክም ፡ ተናዘህ ፡ እረፈው
በደሙ ፡ ያጥበዋል ፡ ለኢየሱስ ፡ ንገረው

አዝ፦ ደስ ፡ ይበልህ ፡ ወንድሜ ፡ ከሳሽህ ፡ ተጥሏል
የኃጢአትህ ፡ ዋጋ ፡ በጌታ ፡ ተከፍሏል
ምህረቱን ፡ ተቀበል ፡ ኃዘንህን ፡ እርሳው
ከንስሐ ፡ ወዲያ ፡ ልብህን ፡ ደስታ ፡ ይሙላው

በእድፋሙ ፡ ልብስህ ፡ ሰውነትህ ፡ ተከድኖ
በአፍረት ፡ ተውጠህ ፡ በደልህ ፡ ተጋኖ
ምንም ፡ ነገር ፡ ቢሆን ፡ "ከቶ ፡ ተስፋ ፡ አልቆርጥም"
ብለህ ፡ ተሟገተው ፡ "ከፀጋው ፡ አልሸሽም"

አዝ፦ ደስ ፡ ይበልህ ፡ ወንድሜ ፡ ከሳሽህ ፡ ተጥሏል
የኃጢአትህ ፡ ዋጋ ፡ በጌታ ፡ ተከፍሏል
ምህረቱን ፡ ተቀበል ፡ ኃዘንህን ፡ እርሳው
ከንስሐ ፡ ወዲያ ፡ ልብህን ፡ ደስታ ፡ ይሙላው

ጠላትህን ፡ ጥሎ ፡ እስራትህን ፡ ቆርጦ
ክስህን ፡ ደምስሶ ፡ ፍርድህን ፡ ለውጦ
ያ ፡ የፍቅር ፡ አምላክ ፡ ምህረትን ፡ አውጇል
ልብስህም ፡ እንዲቀየር ፡ ትዕዛዝን ፡ አውጥቷል

አዝ፦ ደስ ፡ ይበልህ ፡ ወንድሜ ፡ ከሳሽህ ፡ ተጥሏል
የሃጥያትህ ፡ ዋጋ ፡ በጌታ ፡ ተከፍሏል
ምህረትን ፡ ተቀበል ፡ ሃዘንህን ፡ እርሳ
ከንስሃ ፡ ወዲያ ፡ ልብህን ፡ ደስታ ፡ ይሙላው