በፍፁም ፡ ልባቸው ፡ እንዲያገለግሉት (Befetsum Lebachew Endiyagelegelut) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 3:22
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በፍፁም ፡ ልባቸው ፡ እንዲያገለግሉት
በእርሱና ፡ ለእርሱ ፡ ደግሞ ፡ እንዲኖሩለት
ጌታ ፡ ልጆቹን ፡ ያጠራል ፡ ከኃጢአት ፡ ያነጻቸዋል (፪x)

በእንሰሳት ፡ ፋንድያ ፡ ቤቱ ፡ እንደዚያ ፡ ገምቶ
ያን ፡ የጥንቱን ፡ ጠረን ፡ መዓዛውን ፡ አጥቶ
ኢየሱስ ፡ አያስችለውም ፡ ሳያነጻ ፡ አያልፈውም (፪x)

ከቤተ-መቅደስ ፡ ውስጥ ፡ ሸቀጡን ፡ አራግፎ
የሚቸረችረውን ፡ ነጋዴውን ፡ ገርፎ
አስወጥቶ ፡ ያባርራል ፡ ቅንአቱ ፡ ያቃጥለዋል (፪x)

አብሮ ፡ አደግ ፡ እንክርዳድ ፡ ስንዴውም ፡ ሲታጨድ
አስተዋይ ፡ ገበሬ ፡ ያንን ፡ መንሹን ፡ ሲሰድ
ምርቱን ፡ ከግርዱ ፡ ይለያል ፣ ገለባውን ፡ ለእሳት ፡ ይሰጣል (፪x)

በፍፁም ፡ ልባቸው ፡ እንዲያገለግሉት
በእርሱና ፡ ለእርሱ ፡ ደግሞ ፡ እንዲኖሩለት
ጌታ ፡ ልጆቹን ፡ ያጠራል ፡ ከኃጢአት ፡ ያነጻቸዋል (፪x)