አዲስ ፡ ዝማሬ ፡ እንዘምር (Addis Zemarie Enzemer) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 4:15
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ አዲስ ፡ ዝማሬን ፡ እንዘምር
ለመድኃኒታችን ፡ ክብር
የምሥጋናችንን ፡ ሽታ
እናሳርግ ፡ በዕልልታ (፪x)

በእረኛቸው ፡ የታመኑ ፣ በመስኩ ፡ የተሰማሩ
ዱካውን ፡ እየተከተሉ ፣ ለደህንነት ፡ የተጠሩ
ከጨካኝ ፡ አውሬ ፡ የዳኑ ፣ ከመታረድ ፡ የተረፉ
ሃሴትን ፡ እንደሚያደርጉ ፡ በአጥፊው ፡ ጥፋት ፡ ስላልጠፉ
 
አዝ፦ አዲስ ፡ ዝማሬን ፡ እንዘምር
ለመድኃኒታችን ፡ ክብር
የምሥጋናችንን ፡ ሽታ
እናሳርግ ፡ በዕልልታ (፪x)

ማቃችንን ፡ ቀዷልና ፡ ፀጋውን ፡ አልብሶናልና
ክብራችን ፡ ትዘምርለት ፡ ፍቅሩ ፡ አጽናንቶናልና
ጉዳታችንን ፡ የሚሹ ፡ ጉድጓድ ፡ ምሰው ፡ የጠበቁን
አጋንንት ፡ አፍረዋልና ፡ ያደፈጡት ፡ ሊያጠቁን

አዝ፦ አዲስ ፡ ዝማሬን ፡ እንዘምር
ለመድኃኒታችን ፡ ክብር
የምሥጋናችንን ፡ ሽታ
እናሳርግ ፡ በዕልልታ (፪x)

በፍፁም ፡ ልብ ፡ እንዘምር ፣ በአምላካችን ፡ ደስ ፡ ይበለን
እናጨብጭብ ፡ ዕልል ፡ እንበል ፣ ለምንስ ፡ እንቆጥባለን
በምሥጋናችን ፡ ዝማሬ ፡ ምሽጉን ፡ እናፈርሳለን
በመንፈሳዊው ፡ ጦር ፡ ዕቃ ፡ ድል ፡ በድል ፡ እንሄዳለን

አዝ፦ አዲስ ፡ ዝማሬን ፡ እንዘምር
ለመድኃኒታችን ፡ ክብር
የምሥጋናችንን ፡ ሽታ
እናሳርግ ፡ በዕልልታ (፪x)