ቀን ፡ አለ (Qen Ale) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Lyrics.jpg


(6)

ይታይ
(Yetay)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

ያሰቡት ፡ ሳይሰምር ፡ ሲቀር ፡ ሆኖ ፡ እንደህልም
በእኩለ ፡ ቀንም ፡ ላይ ፡ በጊዜ ፡ ሲጨልም (፪x)
በዕድሜ ፡ ያከማቹት ፡ በዋዛ ፡ ሲበተን
በመከራ ፡ እሳት ፡ ማንነት ፡ ሲፈተን (፪x)

ሁኔታውን ፡ ሳይሆን ፡ ቃልህን ፡ አምናለሁ
ታድናለህ ፡ ብዬ ፡ ስንቴ ፡ ዘምሬያለሁ
ወጀቡ ፡ ቢበዛም ፡ በአንተ ፡ ተስፋ ፡ አልቆርጥም
ይዘንባል ፡ እላለሁ ፡ ደመናውን ፡ ባላይም

አዝ፦ (ቀን ፡ አለ) ፡ ፀሐይ ፡ ትወጣለች
(ቀን ፡ አለ) ፡ ይኸ ፡ ሌሊት ፡ ያልፋል
(ቀን ፡ አለ) ፡ የታመንኩት ፡ ጌታ
(ቀን ፡ አለ) ፡ በክብሩ ፡ ይመጣል
(ቀን ፡ አለ) ፡ ፀጋ ፡ ልኮልኛል
(ቀን ፡ አለ) ፡ እሸጋገራለሁ
(ቀን ፡ አለ) ፡ በአስጨነቀኝ ፡ እራስ ፡ ላይ
(ቀን ፡ አለ) ፡ ቆሜ ፡ እዘምራለሁ (፪x)

የሕይወት ፡ ቀመሩ ፡ መውረድና ፡ መውጣት
ነፍሴ ፡ ምድረበዳው ፡ ውጊያው ፡ ቢያሰለቻት
ዓይኖቼ ፡ ሳይወዱ ፡ ተገደው ፡ ቢያለቅሱ
የድል ፡ መዝሙሮቼ ፡ ለዛሬ ፡ ቢረሱ

እንደማያልፍ ፡ የለም ፡ ይህን ፡ ቀን ፡ አልፋለሁ
ጌታዬ ፡ ሲመጣ ፡ በድል ፡ እወጣለሁ
ይህ ፡ ሰው ፡ አበቃለት ፡ ያለው ፡ ጠላቴ ፡ ነው
በቆፈረው ፡ ጉድጓድ ፡ ሲወድቅ ፡ አየዋለሁ

አዝ፦ (ቀን ፡ አለ) ፡ ፀሐይ ፡ ትወጣለች
(ቀን ፡ አለ) ፡ ይሄ ፡ ሌሊት ፡ ያልፋል
(ቀን ፡ አለ) ፡ የታመንኩት ፡ ጌታ
(ቀን ፡ አለ) ፡ በክብሩ ፡ ይመጣል
(ቀን ፡ አለ) ፡ ፀጋ ፡ ልኮልኛል
(ቀን ፡ አለ) ፡ እሸጋገራለሁ
(ቀን ፡ አለ) ፡ ባስጨነቀኝ ፡ እራስ ፡ ላይ
(ቀን ፡ አለ) ፡ ቆሜ ፡ እዘምራለሁ

በወይን ፡ ሃረግ ፡ ፍሬ ፡ ቢታጣ ፡ የሚቀመስ
ምንም ፡ እንኳን ፡ ዛሬ ፡ ባታፈራ ፡ በለስ (፪x)
በጐች ፡ ከማደሪያው ፡ ከበረት ፡ ቢታጡ
እርሾችም ፡ ጠውልገው ፡ መብልን ፡ ባይሰጡ (፪x)

እኔ ፡ ግን ፡ በእግዚአብሔር ፡ በእርሱ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
በከፍታዎችም ፡ ላይ ፡ ያራምደኛል
በመድሃኒቴ ፡ አምላክ ፡ ሃሴት ፡ አደርጋለሁ
ጌታ ፡ እግዚአብሔር ፡ ዘወትር ፡ ሃይሌ ፡ ነው

አዝ፦ (ቀን ፡ አለ) ፡ ፀሐይ ፡ ትወጣለች
(ቀን ፡ አለ) ፡ ይሄ ፡ ሌሊት ፡ ያልፋል
(ቀን ፡ አለ) ፡ የታመንኩት ፡ ጌታ
(ቀን ፡ አለ) ፡ በክብሩ ፡ ይመጣል
(ቀን ፡ አለ) ፡ ፀጋ ፡ ልኮልኛል
(ቀን ፡ አለ) ፡ እሸጋገራለሁ
(ቀን ፡ አለ) ፡ ባስጨነቀኝ ፡ እራስ ፡ ላይ
(ቀን ፡ አለ) ፡ ቆሜ ፡ እዘምራለሁ (፪x)

(ቀን ፡ አለ)