ሚስጥር (Mister) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Tesfaye Chala 5.jpeg


(5)

ይታይ
(Yetay)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

 
ሚስጥር ፡ አለ ፡ ልቤ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ለሰው ፡ ያልነገርኩት (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
አብረውኝ ፡ ለበሉ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ያላጨዋወትኩት (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ዙሪያዬ ፡ ጸጥ ፡ ሲል (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
በሮቼን ፡ ዘግቼ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ልንገረው ፡ ለአምላኬ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
የሆዴን ፡ ገልጬ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
እዩት ፡ ይሄ ፡ ልቤን ፡ እየተሸከመ
ብቻውን ፡ አምቆት ፡ ብቻውን ፡ ታምኖ
ዛሬ ፡ ዙፋኑ ፡ ስር ፡ ሸክሜን ፡ ልጣለው
እስከመቼ ፡ ልዘን ፡ አምላክ ፡ እንደሌለው
ወዳጅ ፡ እንደሌለው

አዝ፦ ደረሰ ፡ ጊዜው ፡ ሰዓቱ ፡ የአምላኬን ፡ ፊት ፡ የማይበት
መንፈሴን ፡ ላዋርድ ፡ እራሴን ፡ ዝቅ ፡ ይበል ፡ ይምበርከክ ፡ ጉልበት
በስውር ፡ የለመንኩትን ፡ በግልጽ ፡ እርሱ ፡ እንደሚከፍለኝ
ሸክሜን ፡ ልጣል ፡ እግሩ ፡ ስር ፡ መጽሃፍ ፡ እንደነገረኝ
(፪x)

ለካስ ፡ አለጉዳይ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ለሰው ፡ የማይነግሩት (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ወይ ፡ በሆድ ፡ ደብቀው (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
የማያባብሉት (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
አምቄ ፡ ደብቄ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
እስከመቼ ፡ ልጐዳ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ልንገረው ፡ በእምባዬ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
ሰምቶ ፡ ለሚረዳ (ሚስጥር ፡ ሚስጥር)
መጐዳቴን ፡ አይቶ ፡ ዘምበል ፡ ይልልናል
ሰምቶ ፡ እንዳልሰማ ፡ መቼ ፡ ጥሎ ፡ ያልፋል
ለእርሱ ፡ እነግረዋለሁ ፡ አልፈልግም ፡ ለሰው
የልቤን ፡ ዘርግፌ ፡ እገላገላለሁ (፪x)

አዝ፦ ደረሰ ፡ ጊዜው ፡ ሰዓቱ ፡ የአምላኬን ፡ ፊት ፡ የማይበት
መንፈሴን ፡ ላዋርድ ፡ እራሴን ፡ ዝቅ ፡ ይበል ፡ ይምበርከክ ፡ ጉልበት
በስውር ፡ የለመንኩትን ፡ በግልጽ ፡ እርሱ ፡ እንደሚከፍለኝ
ሸክሜን ፡ ልጣል ፡ እግሩ ፡ ስር ፡ መጽሃፍ ፡ እንደነገረኝ
(፪x)

አዝ፦ ደረሰ ፡ ጊዜው ፡ ሰዓቱ ፡ የአምላኬን ፡ ፊት ፡ የማይበት
መንፈሴን ፡ ላዋርድ ፡ እራሴን ፡ ዝቅ ፡ ይበል ፡ ይምበርከክ ፡ ጉልበት
በስውር ፡ የለመንኩትን ፡ በግልጽ ፡ እርሱ ፡ እንደሚከፍለኝ
ሸክሜን ፡ ልጣል ፡ እግሩ ፡ ስር ፡ መጽሃፍ ፡ እንደነገረኝ
(፬x)