አምንሃለሁ ፡ ጌታ (Amnehalehu Gieta) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Tesfaye Chala 4.jpg


(4)

የበላይ ፡ ነህ ፡ ጌታ
(Yebelay Neh Gieta)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

አዝ:- አምንሃለሁ ፡ ጌታ ፡ አምንሃለሁ ፡ አምንሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አምንሃለሁ (፪x)
ጭር ፡ ባለው ፡ ደረቅ ፡ ምድረ ፡ በዳ ፡ ውኃ ፡ አፍልቀህልኝ ፡ ጠጥቻለሁ (፪x)
አምንሃለሁ ፡ ጌታ ፡ አምንሃለሁ ፡ አምንሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አምንሃለሁ (፪x)
ጭር ፡ ባለው ፡ ደረቅ ፡ ምድረ ፡ በዳ ፡ ውኃ ፡ አፍልቀህልኝ ፡ ጠጥቻለሁ (፪x)

ጨለማው ፡ እጅግ ፡ በርትቶ
ተስፋ ፡ የሚጣልበት ፡ ጠፍቶ
ግራ ፡ ቀኝ ፡ በሩ ፡ ሲዘጋ
ተጣራሁ ፡ ረዳት ፡ ፍለጋ

ጩኸቴን ፡ ሰምተህ ፡ ከሰማይ
ወርደሃል ፡ በጠላቴ ፡ ላይ
ወጀቡን ፡ ጸጥ ፡ አረክልኝ
ኢየሱስ ፡ ጋሻ ፡ ሆንክልኝ
(፪x)

አዝ:- አምንሃለሁ ፡ ጌታ ፡ አምንሃለሁ ፡ አምንሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አምንሃለሁ (፪x)
ጭር ፡ ባለው ፡ ደረቅ ፡ ምድረ ፡ በዳ ፡ ውኃ ፡ አፍልቀህልኝ ፡ ጠጥቻለሁ (፪x)

ኢየሱስ ፡ የነፍሴ ፡ መድሃኒት
ኢየሱስ ፡ ድንቅ ፡ የሰራኅልኝ
ኢየሱስ ፡ ተራራውን ፡ ንደህ
ኢየሱስ ፡ ሜዳ ፡ አደረክልኝ
ኧረ ፡ አይቻልም ፡ ከእንግዲህስ ፡ አልልም
በዐይኔ ፡ አይቻለሁ ፡ አልጠራጠርም
አንተ ፡ ይሁን ፡ ካልክ ፡ የማይሆን ፡ ይሆናል
ወደደም ፡ ጠላም ፡ ፍጥረት ፡ ይሰማሃል
ጌታ ፡ ነህ (፪x) ፡ ማን ፡ ይቃወምሃል
ባሕሩን ፡ ስትከፍለው ፡ ዐይኖች ፡ አይተውሃል
ጌታ ፡ ነህ (፪x) ፡ ኢየሱስ ፡ ማን ፡ ይቃወምሃል
ባሕሩን ፡ ስትከፍለው ፡ ዐይኖች ፡ አይተውሃል

አዝ:- አምንሃለሁ ፡ ጌታ ፡ አምንሃለሁ ፡ አምንሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አምንሃለሁ (፪x)
ጭር ፡ ባለው ፡ ደረቅ ፡ ምድረ ፡ በዳ ፡ ውኃ ፡ አፍልቀህልኝ ፡ ጠጥቻለሁ (፪x)
አምንሃለሁ ፡ ጌታ ፡ አምንሃለሁ ፡ አምንሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አምንሃለሁ (፪x)
ጭር ፡ ባለው ፡ ደረቅ ፡ ምድረ ፡ በዳ ፡ ውኃ ፡ አፍልቀህልኝ ፡ ጠጥቻለሁ (፪x)