ወጥመዱ ፡ ተሰብሮ ፡ አመለጥኩኝ (Wetmedu Tesebro Ameletkugn) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Lyrics.jpg


(3)

ወጥመዱ ፡ ተሰብሮ ፡ አመለጥኩኝ
(Wetmedu Tesebro Ameletkugn)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 5:13
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

አዝ፦ ወጥመዱ ፡ ተሰብሮ ፡ አመለጥኩኝ
በአምላኬ ፡ ጥላ ፡ ውስጥ ፡ አደርኩኝ
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
እንግዲህ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፪x)

እንግዲህስ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፬x)

ጠላቴ ፡ ሊያጠፋኝ ፡ ሲሸምቅ
የወደኩ ፡ መስሎት ፡ በእኔ ፡ ሊስቅ
ነጋሪት ፡ ሲመታ ፡ ሲያስመታ
እምነቴን ፡ ጉልበቴን ፡ ሊፈታ

ቀና ፡ ብዬ ፡ ባላይ ፡ ኖሮ ፡ ዓይኖቸን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አንስቼ
በጠፋሁ ፡ ነበር ፡ አስካሁን ፡ በሰልፉ ፡ ብዛት ፡ ፈርቼ
ደካማን ፡ የምትረዳ ፡ አምላክ ፡ አኔን ፡ ደርሰህ ፡ እረዳኸኝ
መከራዬን ፡ አሳለፍከው ፡ በኮረብታው ፡ ላይ ፡ አቆምከኝ

አዝ፦ ወጥመዱ ፡ ተሰብሮ ፡ አመለጥኩኝ
በአምላኬ ፡ ጥላ ፡ ውስጥ ፡ አደርኩኝ
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
እንግዲህ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፪x)

እንግዲህስ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፬x)

ጠንክሮ ፡ ብዙ ፡ የፈተነኝ ፡ የማይገፋ ፡ የመሰለኝ
ወደቀ ፡ እንደ ፡ ቀላል ፡ ዕቃ ፡ ሰማሁት ፡ ድንፋታው ፡ ሲያበቃ
ቀና ፡ ብዬ ፡ ስመለከት ፡ ከመከራዬ ፡ ቀን ፡ በላይ
ለካስ ፡ ጌታ ፡ አስቦልኝ ፡ ቤቴን ፡ በበረከት ፡ ሊሞላ
ሸሸገኝ ፡ ከጉያው ፡ ገባሁ ፡ ከጥላው ፡ ሥር ፡ አሳደረኝ
እዘምራለሁ ፡ ለሥሙ ፡ በቤቱ ፡ ስለተመቸኝ

አዝ፦ ወጥመዱ ፡ ተሰብሮ ፡ አመለጥኩኝ
በአምላኬ ፡ ጥላ ፡ ውስጥ ፡ አደርኩኝ
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
እንግዲህ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፪x)

እንግዲህስ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፬x)

ኃይሌ ፡ ነው ፡ እታመነዋለሁ ፡ ክብሬ ፡ ነው ፡ እደገፈዋለሁ
ሞገሴ ፡ የማያሳፍረኝ ፡ በፀጋው ፡ የሚደጋግፈኝ
መከታዬ ፡ ነው ፡ ጋሻዬ ፡ ሥሙን ፡ በእውነት ፡ እጠራዋለሁ
ስንቱን ፡ ሸለቆ ፡ ተራራ ፡ ከኢየሱስ ፡ ጋር ፡ አልፌአለሁ
ከጐኔ ፡ የሚቆም ፡ ዘለዓለም ፡ እንዴ ፡ እንኳን ፡ አላሳፈረኝ
በአምላኬ ፡ ቀን ፡ ወጥቶልኛል ፡ እንግዲህ ፡ ማን ፡ ሊቃወመኝ

አዝ፦ ወጥመዱ ፡ ተሰብሮ ፡ አመለጥኩኝ
በአምላኬ ፡ ጥላ ፡ ውስጥ ፡ አደርኩኝ
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
እንግዲህ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፪x)

እንግዲህስ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፰x)