ጻድቅ ፡ ግን ፡ በእምነት (Tsadeq Gen Bemnet) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Lyrics.jpg


(1)

ባማረ ፡ ቅኔ
(Bamare Qenie)

ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 3:40
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

ሄኖክ ፡ ሞትን ፡ እንዳያይ ፡ በእምነት ፡ ተወሰደ
ኖህ ፡ በምድረ ፡ በዳው ፡ መርከብን ፡ አበጀ
አብረሃም ፡ እርስቱን ፡ ከነዓንን ፡ ወረሰ
ሳራም ፡ በእምነቷ ፡ ኃይሏ ፡ ተመለሰ

አዝ፦ ጻድቅ ፡ ግን ፡ በእምነት ፡ በሕይወት ፡ ይኖራል
የሚታየውን ፡ ሳይሆን ፡ የማይታየውን ፡ ይረዳል
የተስፋውን ፡ ቃል ፡ የሰጠው ፡ የታመነ ፡ ነውና
ደካሞች ፡ በእምነት ፡ ጉልበታችሁ ፡ ይጽና (፪x)

ነፍሱ ፡ ፍፁም ፡ ደክማ ፡ ትንፋሽ ፡ ተሰውሮ
የሚታይ ፡ መመኪያ ፡ ከአፈር ፡ ተቀብሮ
ሥጋ ፡ ደግሞ ፡ ዝሎ ፡ ሞት ፡ ሽታ ፡ ሲሸተው
ጻድቅ ፡ ግን ፡ በእምነት ፡ ከክርስቶስ ፡ ጋር ፡ ነው

አዝ፦ ጻድቅ ፡ ግን ፡ በእምነት ፡ በሕይወት ፡ ይኖራል
የሚታየውን ፡ ሳይሆን ፡ የማይታየውን ፡ ይረዳል
የተስፋውን ፡ ቃል ፡ የሰጠው ፡ የታመነ ፡ ነውና
ደካሞች ፡ በእምነት ፡ ጉልበታችሁ ፡ ይጽና (፪x)

ባሕሩን ፡ በበትር ፡ አሻግሮ ፡ የከፈለ
ውሃን ፡ እንደ ፡ ግድግዳ ፡ ገትሮ ፡ ያቆመ
ዝናብን ፡ ኤልያስ ፡ በእምነት ፡ ከለከለ
እስራኤል ፡ በአምላኩ ፡ ጉልበቱ ፡ አየለ

አዝ፦ ጻድቅ ፡ ግን ፡ በእምነት ፡ በሕይወት ፡ ይኖራል
የሚታየውን ፡ ሳይሆን ፡ የማይታየውን ፡ ይረዳል
የተስፋውን ፡ ቃል ፡ የሰጠው ፡ የታመነ ፡ ነውና
ደካሞች ፡ በእምነት ፡ ጉልበታችሁ ፡ ይጽና (፪x)