ነጋ ፡ ሌሊቱ (Nega Lielitu) - ተመስገን ፡ ማርቆስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተመስገን ፡ ማርቆስ
(Temesgen Markos)

Temesgen Markos 2.jpg


(2)

ኃይል ፡ አለ
(Hail Ale)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2008)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:04
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተመስገን ፡ ማርቆስ ፡ አልበሞች
(Albums by Temesgen Markos)

አዝነጋ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ (፬x)
በሰላም ፡ አደርኩኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
እንደመሸ ፡ አልቀረም ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
በሰላም ፡ አደርኩኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
አንበሶች ፡ አልበሉኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ

"ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ሺህ ፡ ዓመት ፡ ንገሥ !"

የታመንኩት ፡ ጌታ ፡ ያድነኛል ፡ ያልኩት
የአንበሶችን ፡ አፍ ፡ ቆልፎ ፡ አየሁት (፪x)
ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ልንገርህ ፡ አምላኬ ፡ ጀግና ፡ ነው
ተዓምርን ፡ ለማድረግ ፡ ለእርሱ ፡ ሁሉ ፡ ቀላል ፡ ነው
ለጌታ ፡ ቀላል ፡ ነው [1]

አዝነጋ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ (፬x)
በሰላም ፡ አደርኩኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
እንደመሸ ፡ አልቀረም ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
በሰላም ፡ አደርኩኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
አንበሶች ፡ አልበሉኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ

"ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ልንገርህ ፡ ስማኝ !"

ውስጤ ፡ ነገር ፡ አለ ፡ ጌታ ፡ ያስቀመጠዉ
በአስጨነቀህ ፡ ጉዳይ ፡ መፍትሄ ፡ በእኔ ፡ አለ (፪x)
መቃብሬ ፡ ጉድጓድ ፡ በአንበሶች ፡ ማደሪያ
በፍፁም ፡ አይሆንም ፡ አለው ፡ ብዙ ፡ ስራ (፪x) [2]

አዝነጋ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ (፬x)
በሰላም ፡ አደርኩኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
እንደመሸ ፡ አልቀረም ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
በሰላም ፡ አደርኩኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ
አንበሶች ፡ አልበሉኝ ፡ ሌሊቱ ፡ ነጋ ፡ ነጋ

"ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ለአንዴና ፡ ለመጨረሻ ፡ ጊዜ ፡ አድምጠኝ !"

ባለራዕይ ፡ ነኝ ፡ አልበላኝ ፡ አንበሳ
ሰላም ፡ አድሪያለሁ ፡ በእርሱ ፡ የተነሳ
ከጌታ ፡ የተነሳ
አላሳፈረኝም ፡ የአመንኩት ፡ ጌታን ፡ ነው
በላተኛው ፡ ትራስ ፡ ሆኖኝ ፡ አይቻለሁ (፪x) [1]

የዳንኤል ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ ይህን ፡ ሁሉ ፡ የሰራው
ሌቱ ፡ ነግቶልኛል ፡ ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው
የዳንኤል ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ ይህን ፡ ያደረገው
ሌቱ ፡ ነግቶልኛል ፡ ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው

ባለራዕይ ፡ ነኝ ፡ ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው
ውስጤ ፡ ነገር ፡ አለ ፡ ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው
በፍፁም ፡ አልሞትም ፡ ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው
ያወርሰኛል ፡ ገና ፡ ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው

ተራው ፡ የእኔ ፡ ነው (፪x)

  1. 1.0 1.1 ዳንኤል ፮ (Daniel 6)
  2. ዳንኤል ፪ (Daniel 2)