ፋሬስ (Fares) - ተመስገን ፡ ማርቆስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተመስገን ፡ ማርቆስ
(Temesgen Markos)

Temesgen Markos 1.png


(1)

ፋሬስ
(Fares)

ቁጥር (Track):

()


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተመስገን ፡ ማርቆስ ፡ አልበሞች
(Albums by Temesgen Markos)

 
ምድራዊ ፡ ሃሳብ ፡ ይዘህ ፡ የምትኖር ፡ እየጫርክ???
እንደሲዖል ፡ ዘንዶ ፡ ደካማ ፡ ምክር ፡ ሆንክ
ዘመን ፡ መጥቶልሃል ፡ ጥሰህ ፡ እንድትወጣ
በእኔ ፡ ክንፍ ፡ ስር ፡ በረህ ፡ ልትቆም ፡ በከፍታ

አዝ፦ ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ ፡ (አሃሃ)
ፋሬስ ፡ (አሄሄሄ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (አሃሃሃ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ አትደበቅ
ቶሎ ፡ አምልጥ ፡ አትቀመጥ
ስፍራህ ፡ እዚህ ፡ እዛ ፡ አይደለም
ጥሰህ ፡ ውጣ ፣ ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ ለዘለዓለም

ጽኑ ፡ የአጋዥ ፡ ቀንበር ፡ ተጭኖህ ፡ የጐበጥክ
ማን ፡ ያላቅቀኛል ፡ ብለህ ፡ የተጨነክ
ቅባት ፡ ተለቀቀ ፡ ቀንበርን ፡ የሚሰብር
አንተ ፡ እኮ ፡ ፋሬስ ፡ ነህ ፡ ተነስ ፡ ጌታን ፡ አክብር

አዝ፦ ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ ፡ (አሃሃ)
ፋሬስ ፡ (አሄሄሄ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (አሃሃሃ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ አትደበቅ
ቶሎ ፡ አምልጥ ፡ አትቀመጥ
ስፍራህ ፡ እዚህ ፡ እዛ ፡ አይደለም
ጥሰህ ፡ ውጣ ፣ ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ ለዘለዓለም

ሚድያም ፡ አስፈራርቶህ ፡ ተደብቀህ ፡ ያለህ
እግዚአብሔር ፡ ትቶኛል ፡ ብለህ ፡ የተማረርህ
ችግር ፡ ተፈራርቆ ፡ ዝለህ ፡ የደካከምክ
መጣስ ፡ የምትችል ፡ ጽኑና ፡ ሓያል ፡ ነህ

አዝ፦ ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ ፡ (አሃሃ)
ፋሬስ ፡ (አሄሄሄ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (አሃሃሃ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ አትደበቅ
ቶሎ ፡ አምልጥ ፡ አትቀመጥ
ስፍራህ ፡ እዚህ ፡ እዛ ፡ አይደለም
ጥሰህ ፡ ውጣ ፣ ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ ለዘለዓለም

ሃይማኖትና ፡ ወግ ፡ ባህል ፡ ተጭኖህ
ሰው ፡ ምን ፡ ይለኝ ፡ ይሆን ፡ ብለህ ፡ የፈራህ
ዳግም ፡ ልትወለድ ፡ ጥሰህ ፡ እንድትወጣ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ኢየሱስ ፡ ከሰማያት ፡ መጣ

አዝ፦ ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ ፡ (አሃሃ)
ፋሬስ ፡ (አሄሄሄ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (ሆ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ፋሬስ ፡ (አሃሃሃ) ፡ አንተ ፡ ፋሬስ
ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ አትደበቅ
ቶሎ ፡ አምልጥ ፡ አትቀመጥ
ስፍራህ ፡ እዚህ ፡ እዛ ፡ አይደለም
ጥሰህ ፡ ውጣ ፣ ጥሰህ ፡ ውጣ ፡ ለዘለዓለም