እወራረዳለሁ (Eweraredalehu) - ተከስተ ፡ ጌትነት

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተከስተ ፡ ጌትነት
(Tekeste Getnet)

Tekeste Getnet 4.jpg


(4)

እወራረዳለሁ
(Eweraredalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2004)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተከስተ ፡ ጌትነት ፡ አልበሞች
(Albums by Tekeste Getnet)

እስኪ ፡ ልነሳ ፡ ልሂድ ፡ ልያዘው
ተራራማው ፡ ምድር ፡ የእኔው ፡ እኮ ፡ ነው
እርጅና ፡ አያውቀኝ ፡ እድሜ ፡ አይወስነኝ
ዛሬም ፡ እንደጥንቱ ፡ ጉልበታም ፡ ሰው ፡ ነኝ

ልቤ ፡ አ ይደነግጥ ፡ ሁኔታን ፡ አይቶ
ለውጥን ፡ ያመጣል ፡ ጫካ ፡ ውስጥ ፡ ገብቶ
ልቤ ፡ አይደነግጥ ፡ ሁኔታን ፡ አይቶ
ይመነጥራል ፡ ጫካ ፡ ውስጥ ፡ ገብቶ

አዝ፦ አልሰማም ፡ የጠላትን ፡ ዛቻ
እሄዳለሁ ፡ እስከምድር ፡ ዳርቻ
ሰጥቶኛል ፡ ጌታዪ ፡ ከፋፍቶ
ከፊቴ ፡ ማንስ ፡ ሊቆም ፡ ከቶ

አልሰጋም ፡ በጠላቴ ፡ ዛቻ
እሄዳለሁ ፡ እስከምድር ፡ ዳርቻ
ሰጥቶኛል ፡ ጌታዬ ፡ ከፋፍቶ
ከፊቴ ፡ ማንስ ፡ ሊቆም ፡ ከቶ

እልፍ ፡ ልበል ፡ ልሂድ ፡ ልተወው
የደከምኩበትን ፡ ከተመኘኸው
አልሟገትም ፡ የእኔ ፡ ነው ፡ ብዬ
ፈቀቅ ፡ ልበል ፡ መብቴን ፡ ጥዬ

በፊቴ ፡ ወጥቷል ፡ የሚዋጋልኝ
በእርሱ ፡ ላይ ፡ ጥዬ ፡ እወጣለሁኝ
የአባቶች ፡ አምላክ ፡ ላያሳፍረኝ
ርሆቦት ሆኖ፡ በምድር ፡ አሰፋኝ

አዝ፦ አልሰማም ፡ የጠላትን ፡ ዛቻ
እሄዳለሁ ፡ እስከምድር ፡ ዳርቻ
ሰጥቶኛል ፡ ጌታዬ ፡ ከፋፍቶ
ከፊቴ ፡ ማንስ ፡ ሊቆም ፡ ከቶ

አልሰጋም ፡ በጠላቴ ፡ ዛቻ
እሄዳለሁ ፡ እስከምድር ፡ ዳርቻ
ሰጥቶኛል ፡ ጌታዬ ፡ ከፋፍቶ
ከፊቴ ፡ ማንስ ፡ ሊቆም ፡ ከቶ

እስኪ ፡ ልነሳ ፡ ልሂድ ፡ ልያዘው
ተራራማው ፡ ምድር ፡ የእኔው ፡ እኮ ፡ ነው
እርጅና ፡ አያውቀኝ ፡ እድሜ ፡ አይወስነኝ
ዛሬም ፡ እንደጥንቱ ፡ ጉልበታም ፡ ሰው ፡ ነኝ

ልቤ ፡ አይደነግጥ ፡ ሁኔታን ፡ አይቶ
ለውጥን ፡ ያመጣል ፡ ጫካ ፡ ውስጥ ፡ ገብቶ
ልቤ ፡ አይደነግጥ ፡ ሁኔታን ፡ አይቶ
ይመነጥራል ፡ ጫካ ፡ ውስጥ ፡ ገብቶ

አዝ፦ አልሰማም ፡ የጠላትን ፡ ዛቻ (አልሰማም)
እሄዳለሁ ፡ እስከምድር ፡ ዳርቻ (እሄዳለሁ)
ሰጥቶኛል ፡ ጌታዬ ፡ ከፋፍቶ
ከፊቴ ፡ ማንስ ፡ ሊቆም ፡ ከቶ

አልሰጋም ፡ በጠላቴ ፡ ዛቻ (እሄዳለሁ)
እሄዳለሁ ፡ እስከምድር ፡ ዳርቻ
ሰጥቶኛል ፡ ጌታዬ ፡ ከፋፍቶ
ከፊቴ ፡ ማንስ ፡ ሊቆም ፡ ከቶ

ሰምቶ ፡ በእሳት ፡ የሚመልሰው
እርሱ ፡ አምላክ ፡ ተብሎ ፡ ይጠራ
ክርክር ፡ አላውቅበትም
ጊዜ ፡ አልወስድም ፡ ከእናንተ ፡ ጋራ
እጮሃለሁ ፡ ዛሬ ፡ እንደጥንቱ
ይሰማኛል ፡ ስለው ፡ አቤቱ
መሰዊያው ፡ ላይ ፡ በእሳት ፡ ተገልጦ
ይኸው ፡ ይታይ ፡ እርሱ ፡ ከፍ ፡ ብሎ (፪x)

እወራረዳለሁ ፡ በአምላኬ ፡ በሰማይ ፡ ባለው
እወራረዳለሁ ፡ የአባቶቼ ፡ አምላክ ፡ ታማኝ ፡ ነው
እወራረዳለሁ ፡ ቀኑ ፡ አያልቅም/አያልፍም ፡ ጌታ ፡ ሳይታይ
እወራረዳለሁ ፡ አማላኬ ፡ ነው ፡ በምድር ፡ በሰማይ (፪x)