አልመለስም (Alemelesem) - ተፈራ ፡ ነጋሽ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተፈራ ፡ ነጋሽ
(Tefera Negash)

Tefera Negash 1.jpg


(1)

አልመለስም
(Alemelesem)

ዓ.ም. (Year): 2011
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተፈራ ፡ ነጋሽ ፡ አልበሞች
(Albums by Tefera Negash)

የከበረውን ፡ ከተዋረደው ፡ ለይቼ
ዐይኔ ፡ ተገልጦልኝ ፡ አምላኬ ፡ ያየልኝን ፡ አይቼ
ለሕያው ፡ ተስፋ ፡ ተለይቼያለሁ ፡ ወስኜ
ንቄ ፡ ትቼዋለሁ ፡ ዓለማዊነትን ፡ ጨቅኜ

በእውነት ፡ ተረትቻለሁ ፡ በእውነት
ለሕይወት ፡ ተጠርቻለሁ ፡ ለሕይወት
በፍቅር ፡ ተሸንፌአለሁ ፡ በፍቅር
ለክብር ፡ ተለይቻለሁ ፡ ለክብር

(እህም) ፡ መጐናጸፊያ ፡ ወድቆብኝ ፡ (እህ) ፡ እንድከተለው ፡ ጌታዬን
(እህም) ፡ ሞፈር ፡ ቀንበሬን ፡ ሰብሬ ፡ (እህ) ፡ ጨክኜ ፡ ትቼው ፡ እርሻዬን
(እህም) ፡ ምን ፡ ቀረኝ ፡ ብዬ ፡ ልመለስ ፡ (እህ) ፡ የያዝኩት ፡ ከእንቁ ፡ ይበልጣል
(እህም) ፡ ሰው ፡ ክርስቶስ ፡ ተገልጦለት ፡ (እህ) ፡ ዓለምን ፡ እንዴት ፡ ይመርጣል

አዝ፦ አልመለስም ፡ ወደኋላ ፡ አልመለስም (አልመለስም) (፬x)

በሆድ ፡ ሳልረሳ ፡ ከጥንቱ ፡ ያወቀኝ
በእናቴ ፡ ማህጸን ፡ ሳለሁ ፡ የቀደሰኝ
በአስደናቂ ፡ ፍቅሩ ፡ ልቤን ፡ አሸንፎ
ተክሎኛል ፡ በቤቱ ፡ በምክሩ ፡ ደግፎ

የዘለዓለሙን ፡ ተስፋ ፡ ጸንቶ ፡ የሚኖረውን
በእጅ ፡ ያልተዳሰሰ ፡ የሰው ፡ ዐይን ፡ ያላየው
ዋናዬን ፡ አግኝቻለሁ ፡ ከቶ ፡ አልመኝም ፡ ሌላ
ዓለምና ፡ ምኞቱን ፡ አላይም ፡ ወደኋላ

አዝ፦ አልመለስም ፡ ወደኋላ ፡ አልመለስም (አልመለስም) (፬x)

የከበረውን ፡ ከተዋረደው ፡ ለይቼ
ዐይኔ ፡ ተገልጦልኝ ፡ አምላኬ ፡ ያየልኝን ፡ አይቼ
ለሕያው ፡ ተስፋ ፡ ተለይቼያለሁ ፡ ወስኜ
ንቄ ፡ ትቼዋለሁ ፡ ዓለማዊነትን ፡ ጨቅኜ

በእውነት ፡ ተረትቻለሁ ፡ በእውነት
ለሕይወት ፡ ተጠርቻለሁ ፡ ለሕይወት
በፍቅር ፡ ተሸንፌአለሁ ፡ በፍቅር
ለክብር ፡ ተለይቻለሁ ፡ ለክብር (፪x)