እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው (Egziabhier Terarayien Anagerew) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Tamrat Haile 9.jpeg


(9)

እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው
(Egziabhier Terarayien Anagerew)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:01
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው
እንዲህ ፡ አለው (፫x)
"አንተ ፡ ተራራ ! ኧረ ፡ ለመሆኑ ፡ ምንድነህ?
በዘሩባቤል ፡ ፊት ፡ ደልዳላ ፡ ሜዳ ፡ ትሆናለህ"
አለው (፫x) ፡ ናደው ፡ ደለደለው

ከእንግዲህስ ፡ ምን ፡ ሊበጀኝ ፡ እዬዬ ፡ ማለት ፡ ሰለቸኝ
አይደርሰኝም ፡ ወይ ፡ ወረፋ ፡ አይገድህም ፡ ወይ ፡ ስጠፋ
አምላካዊ ፡ መልስ ፡ ከሰማይ ፡ ዘሎ ፡ በኮረብታዎች ፡ ላይ
ዙሪያ ፡ ገባውን ፡ አበራው ፡ ተገፈተረ ፡ ተራራው

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው
እንዲህ ፡ አለው (፫x)
"አንተ ፡ ተራራ ! ኧረ ፡ ለመሆኑ ፡ ምንድነህ?
በልጄ ፡ ፊት ፡ ደልዳላ ፡ ሜዳ ፡ ትሆናለህ"
አለው (፫x) ፡ ናደው ፡ ደለደለው

የኖራ ፡ ሜዳ ፡ ሃውልቱ ፡ ሰባት ፡ እጥፍ ፡ ነዶ ፡ እሳቱ
ሊያጠፋኝ ፡ የተመኘው ፡ ጌታ ፡ በቁጣው ፡ ጐበኘው
ጠላት ፡ ለራሱ ፡ ቆፈረ ፡ ሊያስረኝ ፡ የወጣው ፡ ታሰረ
ሊበላኝ ፡ ያሻው ፡ ተበላ ፡ እኔ ፡ ግን ፡ አለሁ ፡ በተድላ

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው
እንዲህ ፡ አለው (፫x)
"አንተ ፡ ተራራ ! ኧረ ፡ ለመሆኑ ፡ ምንድነህ?
በልጄ ፡ ፊት ፡ ደልዳላ ፡ ሜዳ ፡ ትሆናለህ"
አለው (፫x) ፡ ናደው ፡ ደለደለው

የብዙ ፡ ዘመን ፡ ጠላቴ ፡ ቆሞ ፡ የነበረ ፡ በፊቴ
ብርሃን ፡ እንዳላይ ፡ ከልሎ ፡ አየሁ ፡ በጌታዬ ፡ ተጥሎ
ጌታ ፡ በሰራው ፡ ከበረ ፡ መዝሙር ፡ በአፌ ፡ ጨመረ
ሰማይ ፡ ያጨብጭብ ፡ በደስታ ፡ ምድር ፡ ታክብረው ፡ በእልልታ

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው
እንዲህ ፡ አለው (፫x)
"አንተ ፡ ተራራ ! ኧረ ፡ ለመሆኑ ፡ ምንድነህ?
በዘሩባቤል ፡ ፊት ፡ ደልዳላ ፡ ሜዳ ፡ ትሆናለህ"
አለው (፫x) ፡ ናደው ፡ ደለደለው