አውርቼ ፡ አልጨረስኩም (Awrechie Alchereskum) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Tamrat Haile 9.jpeg


(9)

እግዚአብሔር ፡ ተራራዬን ፡ አናገረው
(Egziabhier Terarayien Anagerew)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 3:30
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

ለአሉባልታ ፡ ጊዜ ፡ የለኝ ፡ እኔ
አውርቼ ፡ አልጨረስኩ ፡ ስለመዳኔ
አልጣላ ፡ ሁሉም ፡ የመጣው ፡ ከአንተ ፡በኋላ

በመቦጫጨቅ ፡ ባርኮት ፡ አይመጣ
ለውኃ ጥማት ፡ ውኃ አይጠጣ
እስኪ ፡ እንጨብጥ ፡ እርፍ ፡ ማረሻ
ሥራ ፡ ነውና ፡ የአገር ፡ መነሻ ፡ አሀ ፡ አሀ

አርሰን ፡ ሳንዘራ ፡ መስከረም ፡ ጠባ
አገር ፡ በወሬ ፡ አትገነባ
ነገም ፡ እንዳያልፍ ፡ እንደ ፡ ትላንቱ
ጉልበት ፡ ማንቃቱ

ከአየር ፡ ከውሃው ፡ ምንም ፡ አላጣን
ስላልሰራን ፡ ነው ፡ ረሃብ ፡ የቀጣን
የሞተው ፡ ሞቶ ፡ ያለነው ፡ አለን
ታጥቀን ፡ ከወጣን ፡ ነገ ፡ እንደርሳለን ፡ አሀአሀ

መስመር ፡ ጠብቆ ፡ ሮጦ ፡ ማሸነፍ
ወይስ ፡ በተንኮል ፡ ወንድምን ፡ መጥለፍ
የትኛው ፡ ይሆን ፡ የተፈቀደው
እኔ ፡ ትቻለሁ ፡ ህሊና ፡ ይፍረድ

እጣ ፡ የደረሰው ፡ ትላንት ፡ ተገፋ
ዛሬስ ፡ ማን ፡ ይሆን ፡ ባለወረፋ
እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እየን ፡ ከሰማይ
የፍቅር ፡ ዘይት ፡ አፍስስ ፡ በእኛ ፡ ላይ

የወሬ ፡ ጠላት ፡ ሥራን ፡ አፍቃሪ
በውኃ በየብስ ፡ በአየር ፡ በራሪ
የትውልድ ፡ ኩራት ፡ መድሃኒተኛ
አምላካችን ፡ ሆይ ፡ አምጣልን ፡ ለእኛ