Tamrat Haile/Egziabhier Awaqi New/Keber Yehunelet

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


ቃሉ ሲያስተምረን መንፈሱ ሲያጽናናን ካቻምናን አለፍን ተሻገርን ፡ አምናን ጠላት ቢቃወመን እጅግ ተገዳድሮ ጌታ ተዋግቶልን ደረስን ዘንድሮ (፪x) አዝ ተራራ ፡ የሚናድለት ፡ ጨለማ ፡ ሚገፈፍለት ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ሚታዘዝለት ኢየሱስ ኢየሱስ ክብር ይሁንለት

መጻተኞች ብንሆን ምድር ያልተገባን ምንም አልጐደለን ለእኛ ከሚረባን ወላጅ እንደሌለው ልጅ አላደረገን የሁላችን አባት እግዚአብሔር ይመስገን (፪x) አዝ ተራራ የሚናድለት ጨለማ ሚገፈፍለት ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ፡ ሚታዘዝለት ኢየሱስ ኢየሱስ ክብር ይሁን

ጉንድሹ ቢመጣ ፡ አካሉ ፡ ተሟልቶ

እውሩ ቢመጣ ሄደ ዓይኑ ተከፍቶ ሙታን ተነስተዋል የተራቡም በሉ እጁን ከዘረጋ ይደርሳል ለሁሉ (፪x) አዝ ተራራ የሚናድለት ጨለማ ሚገፈፍለት ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ሚታዘዝለት ኢየሱስ ኢየሱስ ክብርp ይሁንለት

ሕዝቡ እንደሆነ አይቀር ተስፋውን መውረሱ ፈርዖን ለምን ነው ኃይሉን መጨረሱ ባሕር ተከፈለ በድል ተሻገሩ አንዴ እስከዘለዓለም ተሰብሯል ቀንበሩ (፪x) አዝ ተራራ ፡ የሚናድለት ፡ ጨለማ ፡ ሚገፈፍለት ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ሚታዘዝለት ኢየሱስ ኢየሱስ ክብር ይሁንለት ።