ተሻገሩ ፡ ብሎ (Teshageru Belo) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Lyrics.jpg

፲ ፩
(11)

በድብብቆሽ ፡ ቀኑ ፡ እንዳያልፍ
(Bedebebeqosh Qenu Endayalf)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:29
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

ተሻገሩ ፡ ብሎ ፡ አዞ ፡ በውኃ ፡ ሚያስበላ
ኧረ ፡ እስቲ ፡ ንገሩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ይሆን ፡ ወይስ ፡ ሌላ
መፈጸም ፡ አቅቶት ፡ ከአፉ ፡ የወጣውን ፡ ቃል
ይቅርታ ፡ ጠይቆ ፡ ወይ ፡ ረዳት ፡ ፈልጐ ፡ እርሱ ፡ መች ፡ ያውቃል
ይሄ ፡ ግን ፡ የማውቀው ፡ ጀምሮ ፡ ፈጻሚ
ጠላት ፡ የመጣ ፡ እንደው ፡ እራሱን ፡ አስቀዳሚ
እነርሱን ፡ ተዉአቸው ፡ እኔን ፡ ያዙኝ ፡ የሚል
ከአውሬም ፡ መንጋጋ ፡ በጐቹን ፡ የሚያስጥል

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

ለአብርሃም ፡ ተናግሮ ፡ ነግሮ ፡ ለይሳቅ ፡ አጸና
ለይሳቅ ፡ ተናግሮ ፡ ለያቆብ ፡ ፈጸመ ፡ እርሱ ፡ አይዋሽምና
ዮሴፍ ፡ በግብጽ ፡ ምድር ፡ ቢወርድ ፡ ቢገባም ፡ ተሽጦ
የፈርዖን ፡ መንግሥት ፡ ገዢ ፡ አደረገው ፡ ስርአት ፡ ለውጦ
እግዚአብሔር ፡ ደክሟል ፡ አረጀ ፡ ያለ ፡ ማነው
እኔስ ፡ እስከሚገባኝ ፡ ዛሬም ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነው
የእኔ ፡ እምነት ፡ ቢፈተን ፡ ቢለዋወጥበት
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ ታምኖ ፡ አለ ፡ እዚያው ፡ ባለበት

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

በልዑል ፡ መጠጊያ ፡ አንባ ፡ መሽጐ ፡ ሚኖር
ሁሉንም ፡ በሚችል ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ያድራል ፡ ከቶ ፡ አይሸበርም
ከአዳኞች ፡ ወጥመድ ፡ ከሚያስደነግጥም ፡ ነገር
ከክፉ ፡ ከልሎ ፡ ይታደገው ፡ የለ ፡ ሕያው ፡ እግዚአብሔር
የቀኑ ፡ ፍላጻ ፡ የሌሊቱ ፡ ግርማ ፡ አደጋና ፡ ጋኔል ፡ ተጓዥ ፡ በጨለማ
ሺ ፡ በሺ ፡ ሲያረግፈው ፡ ሲያስረግጠኝ ፡ ኖርኩኝ
እኔም ፡ ከእርሱ ፡ በታች ፡ መቀጥቀጥ ፡ ተማርኩኝ

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው (ጌታ ፡ ነው)
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው (ጌታ)
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው (ጌታ ፡ ነው)
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው (ጌታ ፡ ጌታ ፡ ጌታ)
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው