ድረስልኝ (Dereselegn) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Lyrics.jpg

፲ ፩
(11)

በድብብቆሽ ፡ ቀኑ ፡ እንዳያልፍ
(Bedebebeqosh Qenu Endayalf)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 7:35
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

በጉድለት ፡ ነው ፡ የምመላለሰው
የሞላሁኝ ፡ እመስላለሁ ፡ ለሰው
ያውቀው ፡ የለ ፡ ጌታ ፡ ውስጤን ፡ ዘልቆ
ግብዝነት ፡ የትም ፡ አይሄድ ፡ ርቆ

አዝድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ
ድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ

ቀባብቼ ፡ ውጬዬን ፡ አሳምሬ
ማስመሰሉን ፡ እንጃ ፡ ከየት ፡ ተምሬ
መቅረብ ፡ ትቼ ፡ ሆኜ ፡ እራሴን
አዘገየው ፡ መጐብኘት ፡ ፈውሴን

አዝድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ
ድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ

አውቀዋለሁ ፡ ባሕረ ፡ ገሊላ
አይካድም ፡ አሳም ፡ እንደሞላ
የማጥመድስ ፡ ልምድ ፡ መች ፡ አጥቼ
ልሂድ ፡ እንጂ ፡ ዋናውን ፡ ረስቼ

አዝድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ
ድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ

ወደ ፡ አንተ ፡ እገሰግሳለሁ
ለረድኤት ፡ እጄን ፡ አነሳለሁ
ኧረ ፡ ወዴት ፡ ወዴት ፡ ሊኬድ ፡ ከቶ
የሕይወት ፡ ምንጭ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተን ፡ ትቶ

አዝድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ
ድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ

ይህ ፡ አየነ ፡ ስውር ፡ ደግመህ ፡ ብትዳስሰው
አጥርቶ ፡ አየ ፡ ለይቶ ፡ ዛፍ ፡ ከሰው
ደግመህ ፡ ዳሰኝ ፡ እኔንም ፡ ጌታዬ
እልፍ ፡ ይበል ፡ ይስፋ ፡ እይታዬ

አዝድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ
ድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ

አንተ ፡ ምንጭ ፡ ሆይ ፡ ፍለቅልን ፡ እባክህ
ጠጥተንህ ፡ እንድንባረክ
ለልጆችህ ፡ ላለን ፡ በበረሃ
ፍሰስልን ፡ አንተ ፡ የሕይወት ፡ ውሃ

አዝድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ
ድረስልኝ (፬x) ፡ ምርኮዬን ፡ መልስልኝ