ሌላ ፡ ቃላት ፡ የለኝም (Liela Qalat Yelegnem) - ታጋይ ፡ ወልደማርያም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታጋይ ፡ ወልደማርያም
(Tagay Woldemariam)

Lyrics.jpg


(1)

ብዙ ፡ ዘመን ፡ የተሸከመኝ
(Bezu Zemen Yeteshekemegn)

ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:56
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታጋይ ፡ ወልደማርያም ፡ አልበሞች
(Albums by Tagay Woldemariam)

ክብሬን ፡ ሁሉ ፡ ጥዬ ፡ ለአንተ ፡ እሰግዳለሁ
የሽቶዬን ፡ ብልቃጥ ፡ በፊትህ ፡ አሰብራለሁ
አግርህ ፡ ስር ፡ ወድቄ ፡ አገዛልሃለሁ
ላከበርከኝ ፡ ጌታ ፡ ይህም ፡ ሲያንስህ ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ ሌላ ፡ ቃላት ፡ የለኝም ፡ አንተን ፡ የማከብርበት
ግን ፡ አንዲያው ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ በሰጠኸኝ ፡ አንደበት (፪x)

በምንስ ፡ ጀምሬ ፡ በምን ፡ ልጨርሰው
ጌታ ፡ ውለታህን ፡ በምን ፡ ቃል ፡ ልግለጸው
እንዲያው ፡ ዝም ፡ ብዬ ፡ ክብርን ፡ አሰጥሃለሁ
በብዙ ፡ ምሥጋና ፡ ፊትህ ፡ እቀርባለሁ (፪x)

አዝ፦ ሌላ ፡ ቃላት ፡ የለኝም ፡ አንተን ፡ የማከብርበት
ግን ፡ አንዲያው ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ በሰጠኸኝ ፡ አንደበት (፪x)

ኧረ ፡ እኔስ ፡ ምህረትህ ፡ እጅግ ፡ በዝቶልኛል
ብዙ ፡ ኃጢአቴን ፡ ይቅር ፡ ብለኸኛል
በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ እገዛለሁ
በገናዬን ፡ ይዤ ፡ ፊትህ ፡ እዘምራለሁ (፪x)

አዝ፦ ሌላ ፡ ቃላት ፡ የለኝም ፡ አንተን ፡ የማከብርበት
ግን ፡ አንዲያው ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ በሰጠኸኝ ፡ አንደበት (፪x)

እኔም ፡ እንዳከብርህ ፡ አንተ ፡ መርጠኸኛል
በሞገስ ፡ ላይ ፡ ሞገስ ፡ ደርበህልኛል
ሁልጊዜ ፡ በደስታ ፡ አዜምልሃለሁ
ራሴን ፡ ዝቅ ፡ በማድረግ ፡ አንተን ፡ አክብራለሁ (፪x)

አዝ፦ ሌላ ፡ ቃላት ፡ የለኝም ፡ አንተን ፡ የማከብርበት
ግን ፡ አንዲያው ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ በሰጠኸኝ ፡ አንደበት (፪x)