ሞገሴ ፡ ነህ (Mogesie Neh) - ሽመልስ ፡ ፍላቴ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሽመልስ ፡ ፍላቴ
(Shimeles Filate)


(1)

ሞገሴ ፡ ነህ
(Mogesie Neh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፯ (2015)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:05
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሽመልስ ፡ ፍላቴ ፡ አልበሞች
(Albums by Shimeles Filate)

አዝ፦ ሞገሴ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሴ (፪x)
የማልተካው ፡ የማልተወው ፡ በሕይወቴ
ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሴ ፡ የእኔ ፡ ኢየሱሴ
የማልተካው ፡ የማልተወው ፡ በሕይወቴ

ዛሬ ፡ ላየኝ ፡ ላስተዋለኝ ፡ ሰው
እኔ ፡ አልለውም ፡ እጄ ፡ አንዳረገው
እናገራለሁ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ ብዬ
አልደብቀውም ፡ ኢየሱስዬን
   
እርሱ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ ሞገስ ፡ የሆነኝ
ከአፈር ፡ አንስቶ ፡ ክብር ፡ ያሳየኝ
ታናሹን ፡ ሰው ፡ ሊያከብረኝ ፡ ወዶ
ቤቴ ፡ ገባ ፡ ከሰማይ ፡ ወርዶ

በዓይኖችህ ፡ ከታየሁኝ ፡ እኔ ፡ እጆችህ ፡ ከያዙኝ
ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ በምን ፡ እሰጋለሁ
አንተን ፡ ይዣለሁ
አንተን ፡ ያስቀደመ ፡ ሰው
አይጐልም ፡ ከሚያስበው
ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ በምን ፡ ይሰጋል
አንተን ፡ ይዞሃል

አዝ፦ ሞገሴ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሴ (፪x)
የማልተካው ፡ የማልተወው ፡ በሕይወቴ
ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሴ ፡ የእኔ ፡ ኢየሱሴ
የማልተካው ፡ የማልተወው ፡ በሕይወቴ

ምሕረቱ ፡ የረዳው ፡ ሰው
ቸርነቱ ፡ ሰው ፡ ያረገው
እኔ ፡ ነኝ ፡ ያ ፡ ሰው ፡ እኔ ፡ ነኝ
በፍቅሩ ፡ የታደገኝ

አቅም ፡ አጣሁ ፡ ጉልበቴ ፡ ጠፋ
እኔስ ፡ የለኝም ፡ የመኖር ፡ ተስፋ
ብሎ ፡ ለሚል ፡ ጌታ ፡ አለው ፡ መላ
ታሪክ ፡ ከፍቶ ፡ ያሳያል ፡ ሌላ

በዓይኖችህ ፡ ከታየሁኝ ፡ እኔ ፡ እጆችህ ፡ ከያዙኝ
ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ በምን ፡ እሰጋለሁ
አንተን ፡ ይዣለሁ
አንተን ፡ ያስቀደመ ፡ ሰው
አይጐልም ፡ ከሚያስበው
ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ በምን ፡ ይሰጋል
አንተን ፡ ይዞሃል

አዝ፦ ሞገሴ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሴ (፪x)
የማልተካው ፡ የማልተወው ፡ በሕይወቴ
ማረጌ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሴ
የእኔ ፡ ኢየሱሴ
የማልተካው ፡ የማልተወው ፡ በሕይወቴ