ለበጐ ፡ ነው (Lebego New) - ሰናይት ፡ እንግዳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሰናይት ፡ እንግዳ
(Senait Engeda)

Lyrics.jpg


(3)

ኢየሱስ ፡ ትክክል
(Eyesus Tekekel)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 8:04
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሰናይት ፡ እንግዳ ፡ አልበሞች
(Albums by Senait Engeda)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንድ ፡ ሃሳቡም ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ እንዲደረግ ፡ እናውቃለን
ስለዚህ ፡ ጌታን (፫x)
እናመሰግናለን (፪x)

እርሱ ፡ አይሳሳትም ፡ ሁልጊዜ ፡ ልክ ፡ ነው
ደግሞም ፡ የሚሆነው ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ነው
የእኛ ፡ ሃሳብ ፡ ካልሆነ ፡ ይቅር ፡ ምሬታችን
የያዝነውን ፡ ጌታ ፡ መጠራጠራችን (፪x)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንድ ፡ ሃሳቡም ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ እንዲደረግ ፡ እናውቃለን
ስለዚህ ፡ ጌታን (፫x)
እናመሰግናለን

የፀሎት ፡ መልስ ፡ ቢዘገይ ፡ ቢሆንም ፡ ዝምታ
ብዙ ፡ ጥያቄዬ ፡ እንኳን ፡ መልስ ፡ ቢያጣ
የጠራኝ ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ እኔስ ፡ አምነዋለሁ
ስንቱን ፡ አሳልፎኝ ፡ እዚህ ፡ ደርሻለሁ (፪x)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንድ ፡ ሃሳቡም ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ እንዲደረግ ፡ እናውቃለን
ስለዚህ ፡ ጌታን (፫x)
እናመሰግናለን

በለሱን ፡ የጠበቀ ፡ ፍሬዋን ፡ ይበላል
ጌታውን ፡ የሚጠብቅ ፡ ደግሞ ፡ ይከብራል
ብዙ ፡ አድርጐልኛል ፡ እመሰክራለሁ
እናንተም ፡ እመኑት ፡ ደግሜ ፡ እላለሁ (፪x)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንድ ፡ ሃሳቡም ፡ ለተጠሩት
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ እንዲደረግ ፡ እናውቃለን
ስለዚህ ፡ ጌታን (፫x)
እናመሰግናለን

የሚያልፍ ፡ ባይመስልም ፡ በዝቶ ፡ ችግራችን
የራቀ ፡ ቢመስልም ፡ጌታ፡ ከጐናችን
ቆመን ፡ እንጠብቀው ፡ በመጠበቂያችን
ተስፋውን ፡ የሰጠን ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ ጌታችን (፪x)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንድ ፡ ሃሳቡም ፡ ለተጠሩት
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ እንዲደረግ ፡ እናውቃለን
ስለዚህ ፡ ጌታን (፫x)
እናመሰግናለን