ኢየሱስ ፡ ትክክል (Eyesus Tekekel) - ሰናይት ፡ እንግዳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሰናይት ፡ እንግዳ
(Senait Engeda)

Lyrics.jpg


(3)

ኢየሱስ ፡ ትክክል
(Eyesus Tekekel)

ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 5:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሰናይት ፡ እንግዳ ፡ አልበሞች
(Albums by Senait Engeda)

አዝ፦ ቢመች ፡ ባይመች ፡ ቢሞላ ፡ ቢጐድልም
ብትሰጥ ፡ ብትከለክል ፡ ብትገል ፡ ብታድን
ሥም ፡ አወጣሁልህ ፡ ብዬ ፡ ትክክል
አሜን ፡ ጌታ ፡ ትክክል (፪x)

የበጐቹ ፡ መብዛት ፡ የላሞች ፡ መርባት
የርሻው ፡ መብልን ፡ መስጠት ፡ ጐተራው ፡ መሙላት
ሁሉም ፡ ተስብስቦ ፡ ቢከብ ፡ በዙሪያዬ
የሚያህልህ ፡ የለም ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ

አዝ፦ ቢመች ፡ ባይመች ፡ ቢሞላ ፡ ቢጐድል
ብትሰጥ ፡ ብትከለክል ፡ ብትገል ፡ ብታድን
ሥም ፡ አወጣሁልህ ፡ ብዬ ፡ ትክክል
አሜን ፡ ጌታ ፡ ትክክል

መለኪያዬ ፡ ችግር ፡ እይደለም ፡ ማጣት
ወይ ፡ አግኝቶ ፡ መክበር ፡ ምድራዊ ፡ ሃብት
ለእኔ ፡ ሚበጀውን ፡ ከአንተ ፡ ይልቅ ፡ ማን ፡ ያውቃል
ነፍስን ፡ ከመስጠት ፡ ሁሉስ ፡ መች ፡ ይበልጣል

አዝ፦ ቢመች ፡ ባይመች ፡ ቢሞላ ፡ ቢጐድልም
ብትሰጥ ፡ ብትከለክል ፡ ብትገል ፡ ብታድን
ሥም ፡ አወጣሁልህ ፡ ብዬ ፡ ትክክል
አሜን ፡ ጌታ ፡ ትክክል

ብሩንና ፡ ወርቁን ፡ ዓለምስ ፡ መች ፡ አታ
እርካታ ፡ አጣች ፡ እንጂ ፡ ሰጭውን ፡ እረስታ
ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ የሕይወቴ ፡ ጌታ
ቢሞላ ፡ ቢጐድል ፡ ሆንክልኝ ፡ ደስታ

አዝ፦ ቢመች ፡ ባይመች ፡ ቢሞላ ፡ ቢጐድልም
ብትሰጥ ፡ ብትከለክል ፡ ብትገል ፡ ብታድን
ሥም ፡ አወጣሁልህ ፡ ብዬ ፡ ትክክል
አሜን ፡ ጌታ ፡ ትክክል

የጸሎቴ ፡ መልሱ ፡ ቢዘገይም ፡ ፈውሴ
አንተ ፡ ካየህልኝ ፡ ተስማማሁ ፡ ኢየሱሴ
በጨለማው ፡ ስልጣን ፡ ጭንቅላት ፡ ላይ ፡ ቁሜ
እባርክሃለሁ ፡ ደግሜ ፡ ደግሜ

አዝ፦ ቢመች ፡ ባይመች ፡ ቢሞላ ፡ ቢጐድልም
ብትሰጥ ፡ ብትከለክል ፡ ብትገድል ፡ ብታድን
ሥም ፡ አወጣሁልህ ፡ ብዬ ፡ ትክክል
አሜን ፡ ጌታ ፡ ትክክል