አይቼዋለሁ (Ayechewalehu) - ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል
(Samuel Tesfamichael)

Samuel Tesfamichael 1.jpg


(1)

የሚገርመኝ ፡ መዳኔ ፡ ነው
(Yemigermegn Medanie New)

ዓ.ም. (Year):
"1995" is not in the list (፲ ፱ ፻ ፹ ፩, ፲ ፱ ፻ ፹ ፪, ፲ ፱ ፻ ፹ ፫, ፲ ፱ ፻ ፹ ፬, ፲ ፱ ፻ ፹ ፭, ፲ ፱ ፻ ፹ ፮, ፲ ፱ ፻ ፹ ፯, ፲ ፱ ፻ ፹ ፰, ፲ ፱ ፻ ፹ ፱, ፲ ፱ ፻ ፺ ፩, ...) of allowed values for the "ዓመተምህረት" property.
(2003)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 4:38
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Tesfamichael)

ምህረትህ ፡ ጌታዬ ፡ ምህረትህ
ምህረትህ ፡ አምላኬ ፡ ምህረትህ
ከአንተ ፡ የተነሳ ፡ ነው
ለዚህ ፡ መድረሴ (፬x)

ምህረትህ ፡ እንዴት ፡ በዝቷል
ከፍ ፡ ብሏል ፡ ለእኔስ ፡ ገኗል (፪x)

በበደሉ ፡ ምክንያት ፡ ጠፍቶ ፡ የነበረው ፡ ሰው
ከጥፋት ፡ ጐዳና ፡ በፍቅርህ ፡ መለስከው
የክህነቱን ፡ ስራ ፡ ኑሮው ፡ አድርጐታል
ያዳነውን ፡ አምላኩን ፡ ሁሌ ፡ ይቀድሰዋል (፪x)
ምህረትህ (፬x) ፡ ለእኔ ፡ በዝቷል
ምህረትህ (፬x) ፡ ለእኔ ፡ በዝቷል

ብብዙዎችም ፡ መካከል (አመሰግንሃለሁ)
ቸርነትህ ፡ ምድርን ፡ ሞልቷል (እዘምረዋለሁ)
የስምህ ፡ ትርጉም ፡ ገብቶኛል (ሁሌ ፡ እጠራዋለሁ)

ብብዙዎችም ፡ መካከል (አመሰግንሃለሁ)
ቸርነትህ ፡ ምድርን ፡ ሞልቷል (እዘምረዋለሁ)
ኢየሱስ ፡ ማለት ፡ ገብቶኛል (ሁሌ ፡ እጠራዋለሁ)

ንጉሥ ፡ ንጉሥን ፡ ሲሽረው
ኃያል ፡ ኃያሉን ፡ ሲያወርደው
ጊዜው/አንዱ ፡ ሲያልፍ ፡ ሲተካ ፡ በሌላ ፡ ጌታ
ኢየሱስ ፡ ግን ፡ ሁሌ ፡ የጌቶች ፡ ጌታ (፪x)

አይቼዋለሁ ፡ ኦሆሆ ፡ እኔም ፡ በኑሮዬ ፡ አሃሃ
አመታት ፡ አለፉ ፡ አላለፈም ፡ ጌታዬ
አይቼዋለሁ ፡ ኦሆሆ ፡ እኔም ፡ በኑሮዬ ፡ አሃሃ
ዘመናት ፡ አለፉ ፡ አላለፈም ፡ ጌታዬ
አይቼዋለሁ ፡ ኦሆሆ ፡ እኔም ፡ በኑሮዬ ፡ አሃሃ
ኃያላን ፡ አለፉ ፡ አላለፈም ፡ ጌታዬ
አይቼዋለሁ ፡ ኦሆሆ ፡ እኔም ፡ በኑሮዬ ፡ አሃሃ
ብዙዎች ፡ አለፉ ፡ አላለፈም ፡ ጌታዬ

ሲመሽ ፡ ሲነጋ ፡ ጠዋት ፡ ማታ
አመልከዋለሁ ፡ ይህን ፡ ጌታ (፪x)
ሲመሽ ፡ ሲነጋ ፡ ጠዋት ፡ ማታ
ሾመዋለሁ ፡ በከፍታ (፪x)
ሲመሽ ፡ ሲነጋ ፡ ሁሌ ፡ ማታ
አስበዋለሁ ፡ በመኝታ (፪x)
ሲመሽ ፡ ሲነጋ ፡ ጠዋት ፡ ማታ
እደነቃለሁ ፡ በዚህ ፡ ጌታ (፪x)