የዘለዓለም ፡ ቃልኪዳን (Yezelealem Kalkidan) - ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል
(Samuel Tesfamichael)

Samuel Tesfamichael 3.jpg


(3)

ምሳሌ ፡ የሌለህ
(Misale Yeleleh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 5:31
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Tesfamichael)

በሕይወት ፡ ዘመኔ ፡ አድርጌ ፡ ጓደኛ
የልቤን ፡ ሳዋይህ ፡ ሆነህ ፡ ሚስጥረኛ
በየእለቱ ፡ ችግሬም ፡ በዝቶ ፡ ቢበረታ
ሁኒታውን ፡ ሳላይ ፡ ታመንኩ ፡ በአንተ ፡ ብቻ
አላፈርኩብህም ፡ ዛሬ ፡ አኩርተኀኛል
በድካሜ ፡ ሁሉ ፡ ብርታትን ፡ ሰጥተሃል
አክሊሌ ፡ ሆነህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ታይተሃል
ታማኝ ፡ ነህ ፡ ቃልህን ፡ ፈጽመሃል

አዝ፦ የዘለዓለም ፡ ቃልኪዳን ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ያደረግህ
ሆሆሆሆ ፡ እንዴት ፡ ግሩም ፡ ነህ
ጻድቅ ፡ አምላክ ፡ ነህና ፡ ይኀው ፡ ቃልህን ፡ ፈጸምህ
ሆሆ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ ግሩም ፡ ድንቅ ፡ ነህ

ሆ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
ሆ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
ሆ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
ሆ ፡ ኢየሱስ ፡ ግሩም ፡ ነህ

ሰው ፡ ሰውን ፡ ተማምኖ ፡ ሁልጊዜ ፡ ያፍራል
አንተን ፡ ያመነ ፡ ሰው ፡ ግን ፡ ከቶ ፡ እንዴት ፡ ይወድቃል
ከወንድም ፡ ይልቅ ፡ የምትጠጋጋ
እውነተኛ ፡ ወዳጅ ፡ ከቶም ፡ ማታሰጋ

የውስጤን ፡ አዋቂ ፡ የልቤን ፡ መርማሪ
ሰባራውን ፡ ጠጋኝ ፡ አጋሚ ፡ አስተማሪ
ቃል ፡ ከአፌ ፡ ሳይወጣ ፡ ሳልነግርህ ፡ ሃሳቤን
ታውቀዋለህ ፡ ያለውን ፡ በልቤ

አዝ፦ የዘለዓለም ፡ ቃልኪዳን ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ያደረግህ
ሆሆሆሆ ፡ እንዴት ፡ ግሩም ፡ ነህ
ጻድቅ ፡ አምላክ ፡ ነህና ፡ ይኀው ፡ ቃልህን ፡ ፈጸምህ
ሆሆ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ ግሩም ፡ ድንቅ ፡ ነህ

ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ
ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ
ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ ፡ ሆ
ሆሆሆሆሆ (፬x)

አላፈርኩብህም ፡ ዛሬ ፡ አኩርተኀኛል
በድካሜ ፡ ሁሉ ፡ ብርታትን ፡ ሰጥተሃል
አክሊሌ ፡ ሆነህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ታይተሃል
ታማኝ ፡ ነህ ፡ ቃልህን ፡ ፈጽመሃል

አዝ፦ የዘለዓለም ፡ ቃልኪዳን ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ያደረግህ
ሆሆሆሆ ፡ እንዴት ፡ ግሩም ፡ ነህ
ጻድቅ ፡ አምላክ ፡ ነህና ፡ ይኀው ፡ ቃልህን ፡ ፈጸምህ
ሆሆ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ ፡ እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ በእውነት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ ፡ ግሩም ፡ ድንቅ ፡ ነህ

እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ (፲፩x)