መስቀሉ ፡ በፊቴ (Mesqelu Befitie) - ረዳ ፡ አብርሃም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ረዳ ፡ አብርሃም
(Redda Abraham)

Lyrics.jpg


(1)

አልጥልህም ፡ አልተውህም
(Altelehem Altewehem)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 7:15
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የረዳ ፡ አብርሃም ፡ አልበሞች
(Albums by Redda Abraham)

አዝ፦ መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴ ፡ እንዳይላላ
ሃሌሉ ፡ ሃሌሉ ፡ ሃሌሉያ (፬x)

የቀራንዮን ፡ በግ ፡ ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ
በሁለንተናዬ ፡ ላይም ፡ ሾሜሃለሁ
አልፈራም ፡ አልሰጋም ፡ ወጥቼ ፡ እገባለሁ
ዓለምን ፡ ሰይጣንን ፡ ስልጣኑን ፡ ክጃለሁ

አዝ፦ መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴ ፡ እንዳይላላ
ሃሌሉ ፡ ሃሌሉ ፡ ሃሌሉያ (፬x)

ይህ ፡ የመስቀሉ ፡ ቃል ፡ በዓለም ፡ ለሚኖሩት
ከሞኝነት ፡ ውጭ ፡ አልሆነም ፡ ለሕይወት
ለእኔ ፡ ለምድን ፡ ግን ፡ በርታት ፡ ሆኖልኛል
የተሰራው ፡ ስራ ፡ ሕያው ፡ ሰው ፡ አርጐኛል

አዝ፦ መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
ሃሌሉ ፡ ሃሌሉ ፡ ሃሌሉያ (፬x)

ሁሉን ፡ ፈጽማችሁ ፡ በፊቱ ፡ ለመቆም
የእምነትን ፡ ጋሻ ፡ ታጠቁ ፡ ልበሱ
የሚልን ፡ የድል ፡ ቃል ፡ ይዤ ፡ ልትጋ ፡ ልሩጥ
ጠፍቶ ፡ ከሚያጠፋ ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ ለማምለጥ

አዝ፦ መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
ሃሌሉ ፡ ሃሌሉ ፡ ሃሌሉያ (፬x)

ስለዓለም ፡ ሃጥያት ፡ ነፍሱን ፡ የሰጠውን
መከራና ፡ ስቃይ ፡ የተቀበለውን
እገሰግሳለሁ ፡ ታምኜው ፡ ከልቤ
እያገለገልኩት ፡ በፍፁም ፡ ሃሳቤ

አዝ፦ መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
መስቀሉ ፡ ከፊቴ ፡ ነው ፡ ዓለምም ፡ ከኋላ
ኢየሱስን ፡ ይዣለሁ ፡ ጉልበቴን ፡ እንዳይላላ
ሃሌሉ ፡ ሃሌሉ ፡ ሃሌሉያ (፬x)