ወርቅም ፡ አይተካህም (Werqem Aytekahem) - ናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን
(Nazareth Amanuel Shebsheba Choir)

Nazareth Amanuel Shebsheba Choir 5.jpg


(5)

ፀሐይ ፡ አትጠልቅም ፡ ከቶ ፡ በእኔ ፡ ላይ
(Tsehay Atetelqem Keto Benie Lay)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 6:16
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Nazareth Amanuel Shebsheba Choir)

አንተ ፡ ነህ ፡ ሰላሜ ፡ አንተ ፡ ነህ (፬x)

ወርቅም ፡ አይተካህ
ብርም ፡ አይተካህ
ወዳጅ ፡ አይተካህ (፪x)

ጌትዬ ፡ ምን ፡ እልሃላሁ (፪x)
ሥምህን ፡ እባርካለሁ (፪x)

ብዙ ፡ ሰላም ፡ የሚመስል ፡ አለ ፡ በምድር ፡ ላይ
ከንቱ ፡ ነው ፡ ለጊዜው ፡ ታይቶ ፡ ይጠፋል
አንተ ፡ ግን ፡ የማይናወጥ ፡ ሰላም ፡ አለህ
ከቤትህ ፡ ዘለዓለም ፡ ደስታን ፡ ታጠግባለህ (፪x)

ጌትዬ ፡ ምን ፡ እልሃላሁ (፪x)
ሥምህን ፡ እባርካለሁ (፪x)

ጌታዬ ፡ ለእኔስ ፡ ልዩ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
የውስጤን ፡ የሚያውቅልኝ ፡ እንደ ፡ አንተ ፡ የለም
ሃሳቤን ፡ የልቤን ፡ ቀርበኸኝ ፡ ታውቃለህ
ከሩቁ ፡ መንገዴን ፡ አንተ ፡ ታቀናለህ (፪x)

ደስ ፡ ይለኛል ፡ በአንተ ፡ ጌታዬ
ሃሴትን ፡ ሞልተሃል ፡ በውስጤ (፪x)

አንተ ፡ ብቻ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ጌታ (፬x)

ሌላ ፡ ሌላው ፡ ከንቱ ፡ ነው ፡ ሌላው
ሌላ ፡ ሌላዉ ፡ ሰነፍ ፡ ነው ፡ ሌላዉ (፪x)

እኔ ፡ ጌታ ፡ ምለው ፡ ጌታ ፡ የሆነውን
ልቤ ፡ የፈቀደው ፡ የተቀበለውን (፪x)

ጌታ ፡ ነዉ (፰x)

አንተ ፡ ብቻ ፡ በሰማይ ፡ ጌታ
አንተ ፡ ብቻ ፡ በምድር ፡ ጌታ (፪x)

ሌላ ፡ ሌላው ፡ ከንቱ ፡ ነው ፡ ሌላው
ሌላ ፡ ሌላው ፡ ሰነፍ ፡ ነው ፡ ሌላው (፪x)