ቅንነት (Qenenet) - ናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን
(Nazareth Amanuel Shebsheba Choir)

Nazareth Amanuel Shebsheba Choir 5.jpg


(5)

ፀሐይ ፡ አትጠልቅም ፡ ከቶ ፡ በእኔ ፡ ላይ
(Tsehay Atetelqem Keto Benie Lay)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 6:27
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Nazareth Amanuel Shebsheba Choir)

ቅንነት ፡ ተገኝቶብኝ ፡ አይደል
ጌታዬ ፡ እኔን ፡ የወደደው
ግን ፡ ከምህረቱ ፡ የተነሳ
ቆሜያለሁ ፡ ስሙን ፡ ላነሳ (፪x)

ያለፈውን ፡ ዘመን ፡ ሲያስታውሰው ፡ ልቤ
በህልም ፡ ይመስለኛል ፡ ያለፍኩት ፡ በሃሳቤ
መልካሙን ፡ ቀን ፡ ያየ ፡ እግዚአብሔር ፡ የረዳው
ደግሞ ፡ ከፈል ፡ ይላል ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ አይነቱ ፡ ሰው
መልካሙን ፡ ቀን ፡ ያየ ፡ እግዚአብሔር ፡ የረዳው
ደግሞ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ይላል ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ አይነቱ ፡ ሰው (፪x)

አጋዥ ፡ በሌለበት ፡ ደረቅ ፡ ምድረ ፡ በዳ
አጋዥ ፡ ትሆናለህ ፡ ብቻውን ፡ ለተጐዳ
የሃሩሩን ፡ ሙቀት ፡ በጥላህ ፡ ከልክለህ
ስንቱ ፡ ቀን ፡ ወጣብህ ፡ ስንቱ ፡ ተከለለ (፪x)

ትከሻህ ፡ ለእኔ ፡ ሁሉ ፡ ምቹ ፡ ነው
ከፍ ፡ በል ፡ ምለህ ፡ ቀን ፡ ወጥቶልኝ ፡ ነው (፪x)
ከቶ ፡ አልሰጋም ፡ ምን ፡ እሆን ፡ ብዬ
እኖራለሁ ፡ ተደላድዬ
(፪x)
እኖራለሁ ፡ ተደላድዬ (፬x)

እንደትላንትናው ፡ መስሎት
ጠላቴ ፡ ቢወጣ ፡ ፈጥኖ (፪x)
በመንገዴ ፡ አንተ ፡ ቀድመሃል
ለጥያቄው ፡ መልስ ፡ ሰጥተሃል
ጥያቄው ፡ መልስ ፡ ሰጥተሃል (፪x)

ከእንግዲህ ፡ ላልሰጋ ፡ ልቤም ፡ ላይፈራ
እግዚአብሔር ፡ አምላኬ ፡ ሆኗል ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
በተከበበ ፡ ከተማ ፡ ምህረቱን ፡ ለእኔ ፡ አሰማ
በተከበበ ፡ ከተማ ፡ ምህረቱን ፡ ለእኔ ፡ አሰማ
ረዳቴ ፡ ከፍ ፡ ይበልልኝ (፬x)

በከበበው ፡ ከተማ ፡ ምህረቱን ፡ ለእኔ ፡ አሰማ (፪x)
ረዳትዬ ፡ ከፍ ፡ ይበልልህ (፬x)
በከበበው ፡ ከተማ ፡ ምህረቱን ፡ ለእኔ ፡ አሰማ (፪x)
ረዳትዬ ፡ ከፍ ፡ ይበልልህ (፬x)