ለምንድነው ፡ የሚንኖረው (Lemendenew Yemenenorew) - መስከረም ፡ ጌቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስከረም ፡ ጌቱ
(Meskerem Getu)

Meskerem Getu 2.jpg


(2)

መንግሥትህ ፡ ትምጣ
(Mengesteh Temta)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፰ (2016)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:51
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስከረም ፡ ጌቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Meskerem Getu)

ሰው ፡ ሰው ፡ የሆነበት ፡ የሚኖርበት ፡ ምክንያት ፡ ካልገባው
በአካል ፡ ኖረ ፡ እንጂ ፡ የነፍሱን ፡ ክፍተት ፡ በምን ፡ ሊሞላው
ኑሮን ፡ ለማሸነፍ ፡ እሮጦ ፡ እሮጦ ፡ ቢደርስ ፡ ከግቡ
ተሳካለት ፡ ቢባል ፡ ሃሳቡ ፡ ሞልቶ ፡ እንዲያው ፡ ለደንቡ

ግን ፡ ይሄ ፡ አይደለም ፡ የሕይወት ፡ ትርጉሙ
ከማግኘት ፡ ይበልጣል ፡ ለተፈለጉበት ፡ መገኘት ፡ በውሉ
ሃብትን ፡ ለማካበት ፡ ከመባዘን ፡ ይልቅ
ለምን ፡ እንደምንኖር ፡ በተጋን ፡ ለማወቅ

አዝ፦ ለምንድነው ፡ የምንኖረው
 እስትንፋሳችን ፡ የሚቀጥለው
ዘመን ፡ ሲጨመር ፡ በእድሜያችን ፡ ላይ
ለሰራን ፡ ጌታ ፡ እንድንሰራ ፡ አይደል ፡ ወይ
(፪x)

እርካታ ፡ በገንዘብ ፡ በመብል ፡ መጠጥ ፡ ከተገደበ
በጉብዝናው ፡ ጊዜ ፡ የፈጠረውን ፡ ሰው ፡ ካላሰበ
ኋላ ፡ በእድሜው ፡ ምሽት ፡ እንዳይጸጸት ፡ ከአሁኑ ፡ ይንቃ
የተፈለገበትን ፡ ምክንያት ፡ ያግኝ ፡ ቀኑ ፡ ሳያበቃ

በምድር ፡ ላይ ፡ ያስገኘን ፡ በሰማያት ፡ ያለ
አላማ ፡ ሰጥቶናል ፡ የምንኖርብት ፡ ከቁስ ፡ በዘለለ
ሁሉም ፡ በየድርሻው ፡ በተሰጠው ፡ ስራ
ለመፈጸም ፡ ይሩጥ ፡ የአምላክን ፡ አደራ

አዝ፦ ለምንድነው ፡ የምንኖረው
 እስትንፋሳችን ፡ የሚቀጥለው
ዘመን ፡ ሲጨመር ፡ በእድሜያችን ፡ ላይ
ለሰራን ፡ ጌታ ፡ እንድንሰራ ፡ አይደል ፡ ወይ
(፪x)

ሰው ፡ ሰው ፡ የሆነበት ፡ የሚኖርበት ፡ ምክንያት ፡ ካልገባው
በአካል ፡ ኖረ ፡ እንጂ ፡ የነፍሱን ፡ ክፍተት ፡ በምን ፡ ሊሞላው
ኑሮን ፡ ለማሸነፍ ፡ እሮጦ ፡ እሮጦ ፡ ቢደርስ ፡ ከግቡ
ተሳካለት ፡ ቢባል ፡ ሃሳቡ ፡ ሞልቶ ፡ እንዲያው ፡ ለደንቡ

ግን ፡ ይሄ ፡ አይደለም ፡ የሕይወት ፡ ትርጉሙ
ከማግኘት ፡ ይበልጣል ፡ ለተፈለጉበት ፡ መገኘት ፡ በውሉ
ሃብትን ፡ ለማካበት ፡ ከመባዘን ፡ ይልቅ
ለምን ፡ እንደምንኖር ፡ በተጋን ፡ ለማወቅ

አዝ፦ ለምንድነው ፡ የምንኖረው
 እስትንፋሳችን ፡ የሚቀጥለው
ዘመን ፡ ሲጨመር ፡ በእድሜያችን ፡ ላይ
ለሰራን ፡ ጌታ ፡ እንድንሰራ ፡ አይደል ፡ ወይ
(፫x)