እልፍ ፡ እልፍ (Elef Elef) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu 3.png


(3)

ተሻገር ፡ ያለው
(Teshager Yalew)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2004)
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

 
እልፍ ፡ እልፍ ፡ እያልኩኝ ፡ ልሂድ ፡ እንጂ
ይከፈታል ፡ በፊቴ ፡ ያ ፡ ደጅ (፪x)
ይከፈታል ፡ በፊቴ ፡ ያ ፡ ደጅ (፬x)

ተሰብሮ ፡ አየሁኝ ፡ የናሱ ፡ ደጅ
ልሂድ ፡ ልራመድ ፡ የለኝ ፡ ከልካይ
ገና ፡ እሄዳለሁ ፡ ጨለማውን ፡ ጥሼ
እሻገራለሁ ፡ ሁሉን ፡ ረትቼ

እልፍ ፡ እልፍ ፡ እያልኩኝ ፡ ልሂድ ፡ እንጂ
ይከፈታል ፡ በፊቴ ፡ ያ ፡ ደጅ (፪x)
ይከፈታል ፡ በፊቴ ፡ ያ ፡ ደጅ (፬x)

አልሸበር ፡ አልፈራው ፡ ያ ፡ ጠላቴን
ከቦት ፡ የለም ፡ እሳቱ ፡ ማደሪያዬን (፪x)
ከቦት የለም እሳቱ ማደሪያዬን (፬x)

እልፍ ፡ ብዬ ፡ ጉድጓድ ፡ ቆፈርኩኝ
የኋላውን ፡ ትቼ ፡ የፊቴን ፡ ያዝኩኝ
እልፍ ፡ በማለት ፡ ሚገኘው ፡ ደስታ
ለኔስ ፡ ሆነልኝ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ጌታ

እልፍ ፡ እልፍ ፡ እያልኩኝ ፡ ልሂድ ፡ እንጂ
ይከፈታል ፡ በፊቴ ፡ ያ ፡ ደጅ (፪x)
ይከፈታል ፡ በፊቴ ፡ ያ ፡ ደጅ(፬x)

መሸ ፡ ነጋ ፡ አትልም ፡ አንተ ፡ ስትሰራ
ጨለማ ፡ አይዝህ ፡ እየሱስ ፡ የኔ ፡ ጀግና
የይሁዳ ፡ አንበሳ ፡ የጌቶቹ ፡ ጌታ
የትንሳዔው ፡ ንጉስ ፡ የሱስ ፡ የኔ ፡ አለኝታ (፪x)
ክበር ፡ የኔ ፡ አለኝታ (፪x)

ለቆልኛል ፡ ከአርያም ፡ መንፈሱን
አፈሰሰው ፡ ጌታዬ ፡ ቅባቱን (፪x)
አፈሰሰው ጌታዬ ቅባቱን (፬x)

መሸ ፡ ነጋ ፡ አትልም ፡ አንተ ፡ ስትሰራ
ጨለማ ፡ አይዝህ ፡ እየሱስ ፡ የኔ ፡ ጀግና
የይሁዳ ፡ አንበሳ ፡ የጌቶቹ ፡ ጌታ
የትንሳዔው ፡ ንጉስ ፡ የሱስ ፡ የኔ ፡ አለኝታ (፪x)

ክበር የኔ አለኝታ (የኔ አለኝታ)
ክበር የኔ አለኝታ (ኦ የኔ አለኝታ)
ክበር የኔ አለኝታ (ኢየሱስ የኔ ጌታ)
ክበር የኔ አለኝታ (ኦ የኔ አለኝታ)
ክበር የኔ አለኝታ (ኢየሱስ የኔ አለኝታ)