ክብርህን ፡ ላውራ (Kebrehen Lawra) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu Esp.png

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

እንዲሁ ፡ በዋዛ
(Endihu Bewaza)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 3:54
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

የቱን ፡ ጀምሬ ፡ የቱን ፡ ልተወው
ይሄ ፡ ጌታ ፡ ለእኔ ፡ ያደረገው
ያደረገውን ፡ ሳስበው ፡ ሳስበው
ከቁጥር ፡ በላይ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የሆነውን ፡ ሳስበው ፡ ሳስበው
ከቁጥር ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

አቤት ፡ በአንተ ፡ ስንቱን ፡ አለፍኩኝ
የጠላቴን ፡ ጉልበት ፡ ረገጥኩኝ
ጌታ ፡ ለአንተ ፡ ምን ፡ ይሳንሃል
የጠላት ፡ ምሽግ ፡ ገና ፡ ይፈርሳል

ክብርህን ፡ ላውራ ፡ ዛሬም ፡ ነገም
የእስራኤል ፡ ቅዱስ ፡ አንተው ፡ ተባረክ
ብዙ ፡ ስራዬን ፡ አንተ ፡ ሰርተሃል
አመልክህ ፡ ዘንድ ፡ ይገባኛል (፪x)

ከአንተ ፡ በአንተ ፡ በሆነው ፡ ነገር
እዚህ ፡ ደረስኩ ፡ ሥምህ ፡ ይባረክ
ደስታዬ ፡ ይኸው ፡ ፍፁም ፡ ሆነልኝ
አማኑኤል ፡ ክበርልኝ

የቱን ፡ ጀምሬ ፡ የቱን ፡ ልተወው
ይሄ ፡ ጌታ ፡ ለእኔ ፡ ያደረገው
ያደረገውን ፡ ሳስበው ፡ ሳስበው
ከቁጥር ፡ በላይ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የሆነውን ፡ ሳስበው ፡ ሳስበው
ከቁጥር ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)