የአንበሳን ፡ አፍ ፡ የዘጋ (Yeanbesan Af Yezega) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 7.jpg


(7)

የታመንኩትን ፡ አውቃለሁ
(Yetamenkuten Awqalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝ፦ የአንበሳን ፡ አፍ ፡ የዘጋ ፡ ጠላቴንም ፡ የወጋ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ (፪x)

ከትውልዱ ፡ ወሰን ፡ እኩያ ፡ የሌለው
ፊተኛው ፡ ኋለኛው ፡ ዘላለም ፡ የሆነው
የዕውቀት ፡ ማህደር ፡ የሰላም ፡ አለቃ
ኢየሱስ ፡ ለእኔ ፡ የነፍሴ ፡ ጠበቃ

አዝ፦ የአንበሳን ፡ አፍ ፡ የዘጋ ፡ ጠላቴንም ፡ የወጋ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ (፪x)

ፍርሃትን ፡ ከቦ ፡ ችግር ፡ ሲጋርደኝ
አንበሳው ፡ አፍጦ ፡ ሊገለባብጠኝ
ደረሰ ፡ ጌታዬ ፡ የአማልክቶች ፡ አምላክ
ይኸው ፡ ነፃ ፡ ወጣሁ ፡ አምልኬ ፡ ይባረክ

አዝ፦ የአንበሳን ፡ አፍ ፡ የዘጋ ፡ ጠላቴንም ፡ የወጋ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ (፪x)

ዘመን ፡ የማይሸረው ፡ የዘመናት ፡ ጌታ
ሞትንም ፡ ድል ፡ ነስቶ ፡ ሲኦልን ፡ የረታ
ኃያል ፡ የሆነ ፡ ድንቅ ፡ ምርኮን ፡ የሚያመጣ
ለእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ አቻ ፡ ከየት ፡ መጣ

አዝ፦ የአንበሳን ፡ አፍ ፡ የዘጋ ፡ ጠላቴንም ፡ የወጋ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ (፪x)

ፍሙን ፡ አጋግሎ ፡ አሳቱን ፡ አንድዶ
ሊያጠፋኝ ፡ ሲፈልግ ፡ ያ ፡ ቸካኙ ፡ ዘንዶ
ቃል ፡ ኪዳን ፡ የገባው ፡ ደረሰ ፡ ጌታዬ
በረታሁ ፡ ደስ ፡ አለኝ ፡ ተድሶ ፡ ተስፋዬ

አዝ፦ የአንበሳን ፡ አፍ ፡ የዘጋ ፡ ጠላቴንም ፡ የወጋ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ (፪x)