ጌታ ፡ ባለውለታዬ ፡ ነው (Gieta Baleweletayie New) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 7.jpg


(7)

የታመንኩትን ፡ አውቃለሁ
(Yetamenkuten Awqewalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 6:56
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝብዙ (፫x) ምሥጋና ፡ አለኝ ፡ ለአምላኬ ፡ የምሰጠው
ብዙ (፫x) ዝማሬ ፡ አለኝ ፡ ለእርሱ ፡ የምዘምረው (፪x)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ባለ ፡ ውለታዬ ፡ ነው (፬x)

ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ ተነሽ ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔርን ፡ ባርኪ
ዙሪያሽ ፡ በሚሆነው ፡ ከቶ ፡ አትታወኪ
የሁሉ ፡ የበላይ ፡ ገዢ ፡ አምላክ ፡ ነውና
በእርሱ ፡ ደስ ፡ ይበልሽ ፡ ሰዊለት ፡ ምሥጋና (፪x)

አዝብዙ (፫x) ምሥጋና ፡ አለኝ ፡ ለአምላኬ ፡ የምሰጠው
ብዙ (፫x) ዝማሬ ፡ አለኝ ፡ ለእርሱ ፡ የምዘምረው (፪x)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ባለ ፡ ውለታዬ ፡ ነው (፬x)

በገናም ፡ ይነሳ ፡ እኔም ፡ ማልጄ ፡ እነሳለሁ
ለወደደኝ ፡ ለእርሱ ፡ ቅኔ ፡ እቀኛለሁ
አፌን ፡ በምሥጋና ፡ በቅኔ ፡ ለሞላው
የምለው ፡ የለኝም ፡ ከምሥጋና ፡ ሌላ (፪x)

አዝብዙ (፫x) ምሥጋና ፡ አለኝ ፡ ለአምላኬ ፡ የምሰጠው
ብዙ (፫x) ዝማሬ ፡ አለኝ ፡ ለእርሱ ፡ የምዘምረው (፪x)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ባለ ፡ ውለታዬ ፡ ነው (፬x)

የኢየሱስን ፡ ማዳን ፡ ነፍሴ ፡ እጅግ ፡ ተውቀዋለች
የመስቀሉን ፡ ፍቅር ፡ አይታ ፡ ተማርካለች
ከድቅድቅ ፡ ጨለማ ፡ ወደ ፡ ድንቅ ፡ ብርሃን
አውጥቶኛልና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፪x)

አዝብዙ (፫x) ምሥጋና ፡ አለኝ ፡ ለአምላኬ ፡ የምሰጠው
ብዙ (፫x) ዝማሬ ፡ አለኝ ፡ ለእርሱ ፡ የምዘምረው (፪x)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ባለ ፡ ውለታዬ ፡ ነው (፬x)

ክብሩ ፡ ሰማያትን ፡ ምድርን ፡ ሁሉ ፡ የሸፈነ
ከአጥናፍ ፡ እስከ ፡ አጥናፍ ፡ ሥሙ ፡ የገነነ
አምላካዊ ፡ ክብሩን ፡ ትቶ ፡ የፈለገኝ
ልሰዋ ፡ ምሥጋና ፡ በዝማሬ ፡ ልቀኝ (፪x)

አዝብዙ (፫x) ምሥጋና ፡ አለኝ ፡ ለአምላኬ ፡ የምሰጠው
ብዙ (፫x) ዝማሬ ፡ አለኝ ፡ ለእርሱ ፡ የምዘምረው (፪x)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ባለ ፡ ውለታዬ ፡ ነው (፬x)