አንነቃነቅም (Aneneqaneqem) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 7.jpg


(7)

የታመንኩትን ፡ አውቃለሁ
(Yetamenkuten Awqewalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 5:03
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝ፦ አንነቃነቅም ፡ እንቆማለን
መሠረታችን ፡ አለት ፡ ነው
ዓለቱም ፡ ኢየሱስ ፡ ክንደ ፡ ብርቱ (፪x)

ማዕበል ፡ ቢነሳ ፡ ወጀብም ፡ ቢመጣ
አይሎ ፡ ቢታይም ፡ የቆመ ፡ ባላንጣ
የሕይወት ፡ መሰረት ፡ ብርቱ ፡ ነው ፡ አለቱ
በእርሱ ፡ አንጸናለን ፡ ብንገባም ፡ ከእሳቱ

አዝ፦ አንነቃነቅም ፡ እንቆማለን
መሠረታችን ፡ አለት ፡ ነው
ዓለቱም ፡ ኢየሱስ ፡ ክንደ ፡ ብርቱ (፪x)

የማዕበሉ ፡ አዛዥ ፡ የሁሉ ፡ ፈጣሪ
ብርቱ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ ፡ የእኛ ፡ ፈጣሪ
እንናገራለን ፡ በእርሱ ፡ እንደፍራለን
በዘላለም ፡ አባት ፡ በጸጋው ፡ እንቆማለን

አዝ፦ አንነቃነቅም ፡ እንቆማለን
መሠረታችን ፡ አለት ፡ ነው
ዓለቱም ፡ ኢየሱስ ፡ ክንደ ፡ ብርቱ (፪x)

ስማ ፡ ዲያብሎስ ፡ ሆይ ፡ የጨለማው ፡ አውራ
እኛ ፡ እንደነግጥም ፡ ብትነዛ ፡ ጉራ
መለከት ፡ ብትነፋ ፡ በዓለም ፡ ብታጮኸው
በዓለት ፡ እንቆማለን ፡ እንተን ፡ በሚፈጨው

አዝ፦ አንነቃነቅም ፡ እንቆማለን
መሠረታችን ፡ አለት ፡ ነው
ዓለቱም ፡ ኢየሱስ ፡ ክንደ ፡ ብርቱ (፪x)

ይሄ ፡ ነው ፡ ሚስጢሩ ፡ የመስቀሉ ፡ ጉልበት
የማይነቃነቅ ፡ ደም ፡ የፈሰሰበት
ክብር ፡ ዋጋ ፡ ያለው ፡ ድንቅ ፡ የጌታችን ፡ ስም
አያሳፍረንም ፡ ሕያው ፡ ነው ፡ ዘላለም

አዝ፦ አንነቃነቅም ፡ እንቆማለን
መሠረታችን ፡ አለት ፡ ነው
ዓለቱም ፡ ኢየሱስ ፡ ክንደ ፡ ብርቱ (፪x)