ደስ ፡ ይለኛል (Des Yelegnal) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
Broom.png ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Lyrics.jpg


()

ምሥጋና ፡ መልካም ፡ ነው
(Mesgana Melkam New)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:22
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝ፦ እኔስ ፡ በጌታዬ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሕይወት ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ ፡ ተስማምቶኛል
ካቻ ፡ አምናን ፡ በድል ፡ አሻግሮኛል
አምናንም ፡ በክንዱ ፡ ደግፎኛል
አሁንም ፡ ከክብር ፡ ወደ ፡ ክብር ፡ ያሸጋግረኛል (፪x)

ጠመዝማዛው ፡ መንገድ ፡ ዳገት ፡ ቁልቁለቱ
ሕይወት ፡ ውጣ ፡ ውረድ ፡ ሲሆን ፡ በየዕለቱ
በሚያፀናው ፡ ክንዱ ፡ በኃይሉ ፡ ደግፎኝ
ቆምኩኝ ፡ በምሥጋና ፡ በእርሱ ፡ ደስ ፡ እያለኝ

አዝ፦ እኔስ ፡ በጌታዬ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሕይወት ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ ፡ ተስማምቶኛል
ካቻ ፡ አምናን ፡ በድል ፡ አሻግሮኛል
አምናንም ፡ በክንዱ ፡ ደግፎኛል
አሁንም ፡ ከክብር ፡ ወደ ፡ ክብር ፡ ያሸጋግረኛል

በዚያ ፡ ምድረበዳ ፡ ሀሩር ፡ በበዛበት
መናን ፡ እያበላህ ፡ እኔን ፡ የመራበት
ከአለቱ ፡ ውኃ ፡ አፍልቆ ፡ ያጠጣኝ
እንዴት ፡ ይረሳኛል ፡ ጌታ ፡ ያረገልኝ

አዝ፦ እኔስ ፡ በጌታዬ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሕይወት ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ ፡ ተስማምቶኛል
ካቻ ፡ አምናን ፡ በድል ፡ አሻግሮኛል
አምናንም ፡ በክንዱ ፡ ደግፎኛል
አሁንም ፡ ከክብር ፡ ወደ ፡ ክብር ፡ ያሸጋግረኛል

በለመለመው ፡ መስክ ፡ የሚያሳድረኝ
በእረፍት ፡ ውኃ ፡ ዘንድ ፡ ሁሌ ፡ የሚመራኝ
መልካም ፡ እረኛ ፡ ነው ፡ የሚያሳጣኝ ፡ የለም
ጌታ ፡ ተስማማቶኛል ፡ ከቶ ፡ አይሰለችም

አዝ፦ እኔስ ፡ በጌታዬ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሕይወት ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ ፡ ተስማምቶኛል
ካቻ ፡ አምናን ፡ በድል ፡ አሻግሮኛል
አምናንም ፡ በክንዱ ፡ ደግፎኛል
አሁንም ፡ ከክብር ፡ ወደ ፡ ክብር ፡ ያሸጋግረኛል

በውጊያ ፡ ዘመኔ ፡ ያራመደኝ ፡ በድል
የጠላቴን ፡ እራስ ፡ ያስረገጠኝ ፡ ልዑል
ከክበር ፡ ወደ ፡ ክብር ፡ ያሸጋግረኛል
አዲስ ፡ ነገር ፡ ሲያደርግ ፡ ዛሬም ፡ ያሳየኛል

አዝ፦ እኔስ ፡ በጌታዬ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሕይወት ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ ፡ ተስማምቶኛል
ካቻ ፡ አምናን ፡ በድል ፡ አሻግሮኛል
አምናንም ፡ በክንዱ ፡ ደግፎኛል
አሁንም ፡ ከክብር ፡ ወደ ፡ ክብር ፡ ያሸጋግረኛል