አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ነገር (Amlakie Yaderegewn Neger) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Lyrics.jpg


()

ምሥጋና ፡ መልካም ፡ ነው
(Mesgana Melkam New)

ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:17
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

ኃጢአተኛ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ብሎ ፡ አይቼ
እንደ ፡ ሊባኖስ ፡ ዛፍ ፡ ለምልሞ ፡ ፈርቼ
ተመልሼ ፡ ከቦታው ፡ ፈለግሁት
እንኳን ፡ እርሱን ፡ ስፍራውን ፡ አጣሁት

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

የክፉ ፡ ኃይል ፡ በቁጣ ፡ ዓይኖቼ ፡ እያየኝ
ጥርሱን ፡ በላዬ ፡ ላይ ፡ ስያንገጫግጭብኝ
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ አይቶ ፡ ስቆበታል
የመትፍያው ፡ ቀን ፡ እንደደረሰ ፡ አውቋል

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

ከመቅደሱ ፡ ከሰማይ ፡ ከፍታ ፡ ላይ ፡ ሆኗል
ወደ ፡ ምድር ፡ በታች ፡ አሽቆልቁሎ ፡ አይቷል
የእስረኞቹን ፡ የጩኸት ፡ ቃል ፡ ሰምቷል
ከሞት ፡ አፋፍ ፡ ከፍርድ ፡ ወጥመድ ፡ ፈቷል

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

ከሰይጣን ፡ ኃይል ፡ የዳንህ ፡ ወገን ፡ ሁሉ ፡ ከሰይፍ
ለሚመጣው ፡ ትውልድ ፡ ጻፍና ፡ አስተላልፍ
አምላካችን ፡ ይህን ፡ ተአምር ፡ ሰርቷል
እኔም ፡ ባወራ ፡ ባወራው ፡ በዝቷል

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)