ክብሩ ፡ ይስፋ (Kebru Yesfa) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 1.jpg


(1)

እንዴት ፡ ድንቅ ፡ አምላክ ፡ ነው
(Endiet Denq Amlak New)

ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 2:22
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

የማልወጣው ፡ ይመስለኝና
እምነቴ ፡ ፍፁም ፡ ይከዳኝና
ደንግጬ ፡ ሳለሁ ፡ በሥጋት ፡ ስፈርስ
አይዞህ ፡ ይለኛል ፡ ኢየሱስ

አዝ፦ ክብሩ ፡ ይስፋ ፡ ለመድኃኒዓለም (፬x)

የታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ብዬ ፡ ስናገር
ማየት ፡ ሲሳነኝ ፡ ዓይኔ ፡ ሲታወር
ብርሃን ፡ ሆኖ ፡ ሁሉን ፡ ሊያሳየኝ
ኢየሱስ ፡ ብቅ ፡ ሲል ፡ ይኸው ፡ ታየኝ

አዝ፦ ክብሩ ፡ ይስፋ ፡ ለመድኃኒዓለም (፬x)

ያለፈው ፡ ውለታ ፡ ትጋቱ ፡ ሁሉ
ቢዘነጋልኝ ፡ ያ ፡ ብርታት ፡ ኃይሉ
መፍገምገም ፡ ይዞት ፡ ጠላቴ ፡ ሲያዝ
ኢየሱስ ፡ ብቅ ፡ አለ ፡ እኔን ፡ ሊያግዝ

አዝ፦ ክብሩ ፡ ይስፋ ፡ ለመድኃኒዓለም (፬x)

ፍቅሩ ፡ የሚጣፍጥ ፡ ልዩ ፡ ነውና
ትዕግሥቱም ፡ ፍፁም ፡ አያልቅምና
አቻ ፡ የሚሆነው ፡ የለውምና
ለኢየሱስ ፡ ይሁን ፡ ምሥጋና

አዝ፦ ክብሩ ፡ ይስፋ ፡ ለመድኃኒዓለም (፬x)