የእግዚአብሔር ፡ ክንድ ፡ ሆይ (YeEgziabhier Kend Hoy) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:51
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

አዝየእግዚአብሔር ፡ ክንድ ፡ ሆይ ፡ ተነስ (፫x) ፡ በእኛ
ከጥንት ፡ የነበረው ፡ ያ ፡ ታላቅ ፡ ግሩም ፡ ሃይል
ዛሬም ፡ ይንቀሳቀስ ፡ በእኛ (፪x)

ለእስራኤላውያን ፡ የእሳት ፡ ታንኩናቸው
በደመና ፡ ጋርደስ ፡ ከክፉ ፡ አዳንካቸው
እናምናለን ፡ በሃይልህ ፡ በቃልህ
እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ ተነስ ፡ ሃይልህ ፡ ይፍሰስ

አዝየእግዚአብሔር ፡ ክንድ ፡ ሆይ ፡ ተነስ (፫x) ፡ በእኛ
ከጥንት ፡ የነበረው ፡ ያ ፡ ታላቅ ፡ ግሩም ፡ ሃይል
ዛሬም ፡ ይንቀሳቀስ ፡ በእኛ (፪x)

በምድረበዳ ፡ ቢራቡ ፡ መናን ፡ መግበህ ፡ ጠገቡ
ደግሞም ፡ እንዳይጠማቸው ፡ አስበህ
ከአለት ፡ ውሃን ፡ አፈለቅህ
ልብሳቸው ፡ ነበር ፡ ጌታቸው ፡ ጉልበት ፡ መጠጊያ ፡ ሃይላቸው

አዝየእግዚአብሔር ፡ ክንድ ፡ ሆይ ፡ ተነስ (፫x) ፡ በእኛ
ከጥንት ፡ የነበረው ፡ ያ ፡ ታላቅ ፡ ግሩም ፡ ሃይል
ዛሬም ፡ ይንቀሳቀስ ፡ በእኛ (፪x)

በሙሴ ፡ ውስጥ ፡ ሆነህ ፡ የሰራህ
የኤልያስ ፡ አምላክ ፡ ወዴት ፡ ነህ
አልረሳንም ፡ ከቶ ፡ ተስፋህን
እንደምሰጠን ፡ ሃይልህን

አዝየእግዚአብሔር ፡ ክንድ ፡ ሆይ ፡ ተነስ (፫x) ፡ በእኛ
ከጥንት ፡ የነበረው ፡ ያ ፡ ታላቅ ፡ ግሩም ፡ ሃይል
ዛሬም ፡ ይንቀሳቀስ ፡ በእኛ (፪x)