የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ (Yeadis Kidan Beg) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 3:56
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

አዝ፦ የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ ፡ ቅዱስ ፡ ካህን
የጽድቅ ፡ ንጉሥ ፡ የዓለም ፡ መድህን
የእውነተኛይቱ ፡ ድንኳን ፡ አገልጋይ
ቅዱስ ፡ ካህን ፡ አለን ፡ በላይ ፡ በሰማይ (፪x)

ከብዶ ፡ የነበረው ፡ የህግ ፡ ጭነት
ፍጥረትን ፡ ሲያስጨንቅ ፡ ስለ ፡ ኀጢአት
የህዝብን ፡ ኀጢአት ፡ አንዴ ፡ ለማስጠረግ
ኢየሱስ ፡ ጣቱን ፡ ሰጠ ፡ ለመስቀል ፡ ስቅላት

አዝ፦ የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ ፡ ቅዱስ ፡ ካህን
የጽድቅ ፡ ንጉሥ ፡ የዓለም ፡ መድህን
የእውነተኛይቱ ፡ ድንኳን ፡ አገልጋይ
ቅዱስ ፡ ካህን ፡ አለን ፡ በላይ ፡ በሰማይ (፪x)

የሃጥያት ፡ መጋረጃ ፡ እኛን ፡ የለየንን
ኢየሱስ ፡ ተረተረው ፡ መስዋዕት ፡ ሆኖልን
ቅድስተ ፡ ቅዱሳን ፡ የተስፋው ፡ ሃገር
በእርሱ ፡ ልንገባ ፡ ቻልን ፡ ወደ ፡ ሕይወት ፡ በር

የኮርማ ፡ ደም ፡ መሥዋዕት ፡ ለእኛ ፡ አያስፈልገንም
አንዴ ፡ ተረጭተናል ፡ በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ ደም
ቅዱስ ፡ የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ መካከለኛ
ነፍሱን ፡ ወዶ ፡ ሰጠ ፡ ለሞት ፡ ለእኛ

አዝ፦ የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ ፡ ቅዱስ ፡ ካህን
የጽድቅ ፡ ንጉሥ ፡ የዓለም ፡ መድህን
የእውነተኛይቱ ፡ ድንኳን ፡ አገልጋይ
ቅዱስ ፡ ካህን ፡ አለን ፡ በላይ ፡ በሰማይ (፪x)