መላእክት ፡ አዲስ ፡ ቅኔ (Melaekt Adis Qenie) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 3:49
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

በዙፋኑ ፡ ላይም ፡ በተቀመጠው ፡
በቀኝ ፡ እጁ ፡ ላይ ፡ በውስጥና ፡ በኋላ ፡ የተጻፈበት
በሰባትም ፡ ማኅተም ፡ የተዘጋ ፡ መጽሃፍ ፡ አየሁ ።
ብርቱም ፡ መልአክ ፡ "መጽሃፉን ፡ ይዘረጋ ፡ ዘንድ ፤
ማኅተሞቹንም ፡ ይፈታ ፡ ዘንድ ፡ የሚገባው ፡ ማነው?" ፡
ብሎ ፡ በታላቅ ፡ ድምጽ ፡ ሲያውጅ ፡ አየሁ ።
በሰማይም ፡ ቢሆን ፤ በምድርም ፡ ቢሆን ፤
ከምድርም ፡ በታች ፡ ቢሆን ፤ መጽሃፉን ፡ ሊዘረጋ ፡ ወይም ፡
ሊመለከተው ፡ ማንም ፡ አልተቻለውም ። መጽሃፉንም ፡ ሊዘረጋ ፡
ወይም ፡ ሊመለከተው ፡ የሚገባው ፡ ማንም ፡ ስላልነበረ ፡
እጅግ ፡ አለቀስኩ ። ከሽማግሌዎቹም ፡ አንዱ
"አታልቅስ ፡ እነሆ ፡ ከይሁዳ ፡ ነገድ ፡ የሆነው ፡ አንበሳ ፡
እርሱም ፡ የዳዊት ፡ ስር ፡ መጽሃፉን ፡ ይዘረጋ ፡ ዘንድ ፡
ሰባቱንም ፡ ማኅተም ፡ ይፈታ ፡ ዘንድ ፡ ድል ፡ ነስቷል" ፡ አለኝ ። [1]

መልአክት ፡ አዲስ ፡ ቅኔ ፡ ይዘምራሉ
እንዲህ ፡ እያሉ ፡ መጽሃፍት ፡ ወስደን
ማኅተሞቹን ፡ ትፈታ ፡ ዘንድ ፡ ይገባሃል
ይገባሃል (፫x) ፡ ታርደሃልና ፡ ትፈታ ፡ ዘንድ ፡ ይገባሃል

ሌሎች ፡ ሲሉ ፡ ሰማሁ ፡ የታረደው ፡ በግ
ሃይልና ፡ ባለጠግነት ፣ ጥበብ ፡ ብርታት ፣ ክብር ፡ ምሥጋና ፡ በረከት
ይቀበል ዘንድ ፡ ይገባዋል (፪x) ፡ በረከትን ፡ ይቀበል ፡ ዘንድ ፡ ይገባዋል

በረከት ፡ እና ፡ ክብር ፡ ምሥጋና ፡ ሃይልም
ከዘለዓለም ፡ እስከዘለዓለም ፡ በዙፋኑ ፡ ላይ ፡ ለተቀመጠው ፡ በጉ ፡ ይሁን
ደግሞ ፡ እያሉት ፡ ቅዱሳኑ ፡ ለበጉ ፡ ክብር
ይቀኛሉ ፡ ይዘምራሉ ፡ ያዜማሉ

  1. ራዕይ ፭ ፡ ፩ - ፭ (Revelations 5:1-5)