ጌታ ፡ ሆይ (Gieta Hoy) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 4:58
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

አዝ፦ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ መንገዴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ ሃገር ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ መንገዱ ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ

ታውቃለህ ፡ ጌታ ፡ ጐስቋላነቴን
የማልረባ ፡ ልጅ ፡ መሆኔን
ከእኔ ፡ ጋር ፡ ሆነህ ፡ ካልረዳኽኝ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ደካማ ፡ ነኝ

አዝ፦ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ መንገዴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ ሃገር ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ መንገዱ ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ

የእምነቴ ፡ ድጋፍ ፡ ነህና
ልመርኮዝህ ፡ ጌታዬ ፡ ና
አልመካም ፡ በመቆሜ
ካልሆንክ ፡ አንተ ፡ አጠገቤ

አዝ፦ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ መንገዴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ ሃገር ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ መንገዱ ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ

ዓለማመኔን ፡ እርዳው ፡ ባክህ
በኑሮዬ ፡ እንዳስከብርህ
እምነቴ ፡ ከስራ ፡ ተለይቶ
አንዳልጠፋ ፡ መንገዴ ፡ አንተን ፡ ስቶ

አዝ፦ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ መንገዴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ ሃገር ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ መንገዱ ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ

ሲከፋኝ ፡ አጽናናኝ ፡ መድሃኒቴ
ስደክም ፡ ደግፈኝ ፡ በሕይወቴ
ማን ፡ አለኝ ፡ አለ ፡ አንተ ፡ አለኝታዬ
እስከጽዮን ፡ ድረስ ፡ ጌታዬ

አዝ፦ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ መንገዴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ ሃገር ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን ፡ አደራ
የምሄድበት ፡ መንገዱ ፡ ሩቅ ፡ ነው ፡ አደራ