በችግሬ (Bechegerie) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:14
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

አዝ፦ በችግር ፡ ጓደኛ ፡ በመከራ
አብሮኝ ፡ የሚሰቃይ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
በታናሽነቴ ፡ የማይንቀኝ
ዘመድ ፡ አግኝቻለሁ ፡ የሚወደኝ (፪x)

ኢየሱስ ፡ የሚባል ፡ ድንቅ ፡ መካር
የሰላም ፡ አለቃ ፡ ደግሞም ፡ ፍቅር
የሚባል ፡ ጓደኛ ፡ አግኝቻለሁ
እኔም ፡ በእርሱ ፡ ሰላም ፡ ረክቻለሁ

አዝ፦ በችግር ፡ ጓደኛ ፡ በመከራ
አብሮኝ ፡ የሚሰቃይ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
በታናሽነቴ ፡ የማይንቀኝ
ዘመድ ፡ አግኝቻለሁ ፡ የሚወደኝ (፪x)

ችግሬን ፡ በሙሉ ፡ ወስዶት ፡ እርሱ
ደስታን ፡ ለእኔ ፡ ሰጠኝ ፡ ከመንፈሱ
ሃዘን ፡ ስወርድ ፡ አብሮኝ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
ስደሰትም ፡ አብሮኝ ፡ በተራራ

አዝ፦ በችግር ፡ ጓደኛ ፡ በመከራ
አብሮኝ ፡ የሚሰቃይ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
በታናሽነቴ ፡ የማይንቀኝ
ዘመድ ፡ አግኝቻለሁ ፡ የሚወደኝ (፪x)

ለነፍሱ ፡ ሳይሳሳ ፡ የሞተልኝ
እጅግ ፡ በጣም ፡ አድርጐ ፡ የሚወደኝ
አባት ፡ አግኝቻለሁ ፡ የማይተወኝ
እስከ ፡ ለዘለዓለም ፡ የሚመራኝ

አዝ፦ በችግር ፡ ጓደኛ ፡ በመከራ
አብሮኝ ፡ የሚሰቃይ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
በታናሽነቴ ፡ የማይንቀኝ
ዘመድ ፡ አግኝቻለሁ ፡ የሚወደኝ (፪x)