በዓለም ፡ ከሚገኝ (Bealem Kemigegn) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 4:07
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

አዝ፦ በዓለም ፡ ከሚገኝ ፡ ብዙ ፡ ክብር ፡ ይልቅ
ስለ ፡ ክርስቶስ ፡ መነቀፍን ፡ የሚበልጥ
ብድራቱን ፡ ትኩር ፡ ብሎ ፡ አይቷልና
ሙሴ ፡ ጌታን ፡ አከበረው ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና

ለጊዜው ፡ በኀጢአት ፡ ከሚገኝ ፡ ደስታ ፡ ይልቅ
ለጌታ ፡ መነቀፍ ፡ እጅግ ፡ እንደሚበልጥ
ታውቆት ፡ ክብሩን ፡ ተወ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ተማምኖ
ጌታም ፡ አልተወውም ፡ አየሁ ፡ ልጄ ፡ ብሎ

አዝ፦ በዓለም ፡ ከሚገኝ ፡ ብዙ ፡ ክብር ፡ ይልቅ
ስለ ፡ ክርስቶስ ፡ መነቀፍን ፡ የሚበልጥ
ብድራቱን ፡ ትኩር ፡ ብሎ ፡ አይቷልና
ሙሴ ፡ ጌታን ፡ አከበረው ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና

የማይታየውን ፡ በእምነት ፡ እያየ
የዓለምን ፡ ክብር ፡ ሁሉ ፡ ስለ ፡ ጌታ ፡ ጣለ
ጌታም ፡ አከበረው ፡ ልጁን ፡ አልተወውም
ፀጋን ፡ አለበሰው ፡ ዓለም ፡ የማያየውን

አዝ፦ በዓለም ፡ ከሚገኝ ፡ ብዙ ፡ ክብር ፡ ይልቅ
ስለ ፡ ክርስቶስ ፡ መነቀፍን ፡ የሚበልጥ
ብድራቱን ፡ ትኩር ፡ ብሎ ፡ አይቷልና
ሙሴ ፡ ጌታን ፡ አከበረው ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና

እምነቴን ፡ በስራ ፡ እንድገልጠው
የግለት ፡ መንፈስህን ፡ በሕይወቴ ፡ አብዛው
እስከሞትም ፡ እንኳ ፡ ለስምህ
ለመጋደል ፡ አብቃኝ ፡ እባክህ

አዝ፦ በዓለም ፡ ከሚገኝ ፡ ብዙ ፡ ክብር ፡ ይልቅ
ስለ ፡ ክርስቶስ ፡ መነቀፍን ፡ የሚበልጥ
ብድራቱን ፡ ትኩር ፡ ብሎ ፡ አይቷልና
ሙሴ ፡ ጌታን ፡ አከበረው ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና