የፈሰሰ ፡ ውኃ (Yefesese Weha) - መካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ
(Mekashaw Kassa and Tsebaot Engeda)

Lyrics.jpg


(1)

ዘመን ፡ መጣልኝ
(Zemen Metalegn)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 5:14
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ ፡ አልበሞች
(Albums by Mekashaw Kassa and Tsebaot Engeda)

 
የፈሰሰ ፡ ውኃ ፡ በቃ ፡ አይታፈስም
ዳግመኛ ፡ ሊጠቅም ፡ እድልም ፡ የለውም
ሰው ፡ ተስፋ ፡ ሲቆርጥ ፡ እንዲህ ፡ ይተርታል
የሞተው ፡ ሊቀብር ፡ አልቅሶ ፡ ይወጣል

ጌታ ፡ በአንተ ፡ ዘንድ ፡ የፈሰሰም ፡ ውኃ ዳግም ፡ ይታፈሳል
ኢየሱስ ፡ በአንተ ፡ ዘንድ ፡ ሞቷል ፡ የተባለ ፡ በሕይወት ፡ ይኖራል
ጌታ ፡ በአንተ ፡ ዘንድ ፡ አይቻልም ፡ ሚባል ፡ ቃል ፡ ከቶ ፡ አይገኝም
ኢየሱስ ፡ በአንተ ፡ ዘንድ ፡ የወደቀ ፡ ይነሳል ፡ ተቆርጦ ፡ አይጣልም

አምላኬ ፡ ትችላለህ ፡ ታሪክን ፡ መለወጥ
አምላኬ ፡ ትችላለህ ፡ መራራውን ፡ ማጣፈጥ
ትችላለህ ፡ ታሪክን ፡ መለወጥ
ትችላለህ ፡ መራራውን ፡ ማጣፈጥ

(ኢየሱስ) ፡ ተስፋ ፡ በጠፋበት ፣ (ኢየሱስ) ፡ ተስፋ ፡ ትሆናለህ
(ኢየሱስ) ፡ ታሪክን ፡ በታሪክ ፣ (ኢየሱስ) ፡ ትለዋውጣለህ
(ኢየሱስ) ፡ የጠበቁህ ፡ አያፍሩም ፣ (ኢየሱስ) ፡ በጽናት ፡ የቆዩ
(ኢየሱስ) ፡ በረሃው ፡ ለምልሞ ፣ (ኢየሱስ) ፡ አዲስ ፡ ምዕራፍ ፡ አዩ

አምላኬ ፡ ትችላለህ ፡ ታሪክን ፡ መለወጥ
አምላኬ ፡ ትችላለህ ፡ መራራውን ፡ ማጣፈጥ
ትችላለህ ፡ ታሪክን ፡ መለወጥ
ትችላለህ ፡ መራራውን ፡ ማጣፈጥ

ሞት ፡ ጥላውን ፡ አቅልጦ___፡ ፍርሃት ፡ ሲነግስ
እምነትን ፡ ሊናጠቅ ፡ ጠላት ፡ ሲገሰግስ
የሕይወት ፡ ምዕራፎች ፡ ትግላቸው ፡ በርትቶ
ተስፋ ፡ ያደረጉት ፡ ሳይገኝ ፡ ዘግይቶ

(ጌታ ፡ ያኔማ) ፡ ድንገት ፡ ዘምበል ፡ ስትል ፡ ሁሉም ፡ ይለወጣል
(ኢየሱስ ፡ ያኔማ) ፡ የተመሳቀለው ፡ በቃልህ ፡ ይሰናዳል
(ጌታ ፡ ያኔማ) ፡ ዘመን ፡ ስታመጣ ፡ እስከመቼ ፡ ላሉ
(ኢየሱስ ፡ ያኔማ) ፡ በምሥጋና ፡ ሆነው ፡ ታስበናል ፡ ላሉ

ትችላለህ ፡ ታሪክን ፡ መለወጥ
ትችላለህ ፡ መራራውን ፡ ማጣፈጥ (፪x)