በቃልህ (Beqaleh) - መካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ
(Mekashaw Kassa and Tsebaot Engeda)

Lyrics.jpg


(1)

ዘመን ፡ መጣልኝ
(Zemen Metalegn)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ ፡ አልበሞች
(Albums by Mekashaw Kassa and Tsebaot Engeda)

 
አዝ፦ አልቅበዘበዝም ፡ ከእንግዲህማ
በሥጋ ፡ አልወጣም ፡ ከእንግዲህማ
ግን ፡ በቃልህ ፡ መረቤን/ነገሬን ፡ እጥላለሁ
የተሻለ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ አገኛለሁ (፪x)

እንደ ፡ ቃልህ ፡ መረቤን ፡ እጥላለሁ
የተሻለ ፡ በቃልህ/በጌታ ፡ አገኛለሁ (፪x)

የድካም ፡ ሌሊት ፡ ሆኖ ፡ ሌሊቱ
ለካ ፡ ይፈተናል ፡ ሰውም ፡ ትዕግሥቱ
የራሴን ፡ ጥረት ፡ ሁሉ ፡ ጥሬያለሁ
ታንኳ ፡ መረቤ ፡ ባየው ፡ ባዶ ፡ ነው

አሁንማ ፡ በቃልህ ፡ መረቤን ፡ እጥላለሁ
አሁንም ፡ ሙግቴን ፡ ሁሉ ፡ እተዋለሁ
አሁንማ ፡ የአንተ ፡ ሃሳብ ፡ ይሻላል ፡ እላለሁ
አሁንማ ፡ አየሁት ፡ የእኔማ ፡ ከንቱ ፡ ነው

መቼ ፡ ከጉድጓድ ፡ ጋር ፡ የይሳቅ ፡ ነገሩ
የአምላኩ ፡ ቃልኪዳን ፡ ከእርሱ ፡ ጋር ፡ መኖሩ
በስጥና ፡ በኤሴቅ ፡ ሲያጋፉት ፡ ቢያያቸው
ርሆቦት ፡ ደረሰ ፡ ሁሉን ፡ ትቶላቸው

በረከቴ ፡ ብለው ፡ ጉድጓዱን ፡ ለሚያዩ
አይደለም ፡ አልኳቸው ፡ ከላይ ፡ ነው ፡ ጉዳዩ
ሰው ፡ ቆፍሮ ፡ ያመጣው ፡ ይነቅፋል ፡ ይደርቃል
በቃልህ ፡ የጀመረ ፡ እርሱ ፡ መቼ ፡ ያፍራል

አዝ፦ አልቅበዘበዝም ፡ ከእንግዲህማ
በሥጋ ፡ አልወጣም ፡ ከእንግዲህማ
ግን ፡ በቃልህ ፡ መረቤን/ነገሬን ፡ እጥላለሁ
የተሻለ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ አገኛለሁ (፪x)

እንደ ፡ ቃልህ ፡ መረቤን ፡ እጥላለሁ
የተሻለ ፡ በቃልህ/በጌታ ፡ አገኛለሁ (፪x)

ስለ ፡ እኔ ፡ አውቃለሁ ፡ ሃሳቢ ፡ አልሻም
ውጥኔ ፡ በእጄ ፡ አለው ፡ መድረሻ
ብዬ ፡ ፎክሬ ፡ በራሴ ፡ ትግል
ኋላ ፡ ነቃሁኝ ፡ ስደክም ፡ ስዝል

አሁንማ ፡ ፈቃድህ ፡ ይሆን ፡ እላለሁ
አሁንማ ፡ ከአንተ ፡ የሆነውን ፡ እሻለሁ
አሁንማ ፡ . (1) . ፡ መስገን ፡ እንዳይሆን ፡ እጣዬ
አሁንማ ፡ እንደቃልህ ፡ መረብ ፡ ኑሮዬ

አዝ፦ አልቅበዘበዝም ፡ ከእንግዲህማ
በሥጋ ፡ አልወጣም ፡ ከእንግዲህማ
ግን ፡ በቃልህ ፡ መረቤን/ነገሬን ፡ እጥላለሁ
የተሻለ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ አገኛለሁ (፪x)

መቼ ፡ ከጉድጓድ ፡ ጋር ፡ የይሳቅ ፡ ነገሩ
የአምላኩ ፡ ቃልኪዳን ፡ ከእርሱ ፡ ጋር ፡ መኖሩ
በስጥና ፡ በኤሴቅ ፡ ሲያጋፉት ፡ ቢያያቸው
ርሆቦት ፡ ደረሰ ፡ ሁሉን ፡ ትቶላቸው

በረከቴ ፡ ብለው ፡ ጉድጓዱን ፡ ለሚያዩ
አይደለም ፡ አልኳቸው ፡ ከላይ ፡ ነው ፡ ጉዳዩ
ሰው ፡ ቆፍሮ ፡ ያመጣው ፡ ይነቅፋል ፡ ይደርቃል
በቃልህ ፡ የጀመረ ፡ እርሱ ፡ መቼ ፡ ያፍራል