ደሙ (Demu) - ምህረት ፡ ኢተፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ምህረት ፡ ኢተፋ
(Meheret Etefa)

Meheret Etefa 5.jpg


(5)

ነፍሴ ፡ ወደሱ ፡ አደላ
(Nefsie Wedesu Adela)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 6:03
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የምህረት ፡ ኢተፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Meheret Etefa)

ክበርልኝ...ክበርልኝ

ደሙ ፡ ደሙ ፡ ደሙ
የጌታዬ ፡ ደም ፡ ነው ፡ ደሙ
ደሙ ፡ ደሙ ፡ ደሙ
የኢየሱስ ፡ ደም ፡ ነው ፡ ደሙ
ከኃጢአት ፡ ከበደሌ ፡ የነጻሁበት
እስራቴም ፡ ደግሞ ፡ የተበጠሰበት
በጐልጐታ ፡ ፈሶ ፡ ነጻ ፡ የወጣሁበት
ደሙ ፡ ደሙ ፡ ደሙ
የጌታዬ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ ደሙ
ደሙ ፡ ደሙ ፡ ደሙ
የኢየሱስ ፡ ደም ፡ ነው ፡ ደሙ

አዝ፦ ኦ ፡ የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ
ኦ ፡ የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ
የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ ፡ አመልክሃለሁ

(አሃሃሃ) ቸርነት ፡ ምህረትህን ፡ እያየሁ
(አሃሃሃ) አመልክሃለሁ
(አሃሃሃ) ለእኔ ፡ የሆንከውን ፡ እያየሁ
(አሃሃሃ) አመልክሃለሁ

አዝኜ ፡ ተክዤ ፡ በፍርሃት ፡ እያለሁ
በመስቀልህ ፡ ጉልበት ፡ ድፍረትን ፡ አገኘሁ
የፈሰሰው ፡ ደምህ ፡ ዛሬም ፡ ትኩስ ፡ ነው
ከብዙ ፡ እስራት ፡ ነጻ ፡ ሚያወጣ ፡ ነው
ነጻ ፡ ሚያወጣ ፡ ነው

አዝ፦ ኦ ፡ የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ
ኦ ፡ የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ
የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ ፡ አመልክሃለሁ

(አሃሃሃ) ቸርነት ፡ ምህረትህን ፡ እያየሁ
(አሃሃሃ) አመልክሃለሁ
(አሃሃሃ) ለእኔ ፡ የሆንከውን ፡ እያየሁ
(አሃሃሃ) አመልክሃለሁ

የቀረኝ ፡ ምንድን ፡ ነው ፡ በሕይወቴ ፡ ላይ
የማትፈልገውን ፡ ፈጽሞ ፡ እንዳላይ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ አንሳልኝ ፡ ከሕይወቴ ፡ ላይ
አንተው ፡ ግባበት ፡ በሩጫዬ ፡ ላይ
በሩጫዬ ፡ ላይ

ከዚህ ፡ በላይ ፡ ልኖርልህ ፡ እፈልጋለሁ
ከዚህ ፡ በላይ ፡ ላመልክህ ፡ እፈልጋለሁ
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ንገረኝ ፡ ንገረኝ ፡ ምንድንነው
ኢየሱስ ፡ ጥሩ ፡ እየኖርኩልህ ፡ ነው ፡ ወይ ፡ ስታየኝ
ኢየሱስ ፡ አካሄዴ ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ እስቲ ፡ ንገረኝ (፪x)

አዝ፦ ኦ ፡ የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ
ኦ ፡ የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ
የዓይኖቼ ፡ ማረፊያ ፡ ጌታ ፡ አመልክሃለሁ

(አሃሃሃ) ቸርነት ፡ ምህረትህን ፡ እያየሁ
(አሃሃሃ) አመልክሃለሁ
(አሃሃሃ) ለእኔ ፡ የሆንከውን ፡ እያየሁ
(አሃሃሃ) አመልክሃለሁ