Meheret Etefa/Balegirma/Qenien Eqegnalehu

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ምህረት ኢተፋ ርዕስ ቅኔን እቀኛለሁ አልበም ባለግርማ

አዝ፦ቅኔን እቀኛለሁ ቅኔን እቀኛለሁ
የእጆቹን ሥራ እያየሁ
ትርጉም አለው ለእኔ
ይሄ ሁሉ የማየውን አሃሃሃ
በፊቱ ለማየት እጅግ ናፍቄ
አንጐራጉራለሁ አንጐራጉራለሁ (፪x)


የፈጠራቸውን ፡ ፍጥረቶች ፡ እያየሁ

ጌታን ፡ ከልብ ፡ ሆኜ ፡ አመሰግናለሁ ፦ (፪x)

አቤት ፡ ድንቅ ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ ሥራው አይቆጠር

እዘምራለሁኝ ፡ ለጌታዬ ፡ ክብር ፦ (፪x)


አዝ፦ቅኔን እቀኛለሁ ቅኔን እቀኛለሁ
የእጆቹን ሥራ እያየሁ
ትርጉም አለው ለእኔ
ይሄ ሁሉ የማየውን አሃሃሃ
በፊቱ ለማየት እጅግ ናፍቄ
አንጐራጉራለሁ አንጐራጉራለሁ (፪x)


ውበትን ፡ አገኙ ፡ ሰማያት ፡ በመንፈስህ

የዓለምን ፡ ተራሮች ፡ በቃልህ ፡ አጸናህ ፦ (፪x)

እኔም ፡ ስለነሱ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃልሁ

የፍጥረት ፡ ፈጣሪ :ተባርክ ፡ ብያለሁ ፦(፪x)


አዝ፦ቅኔን እቀኛለሁ ቅኔን እቀኛለሁ
የእጆቹን ሥራ እያየሁ
ትርጉም አለው ለእኔ
ይሄ ሁሉ የማየውን አሃሃሃ
በፊቱ ለማየት እጅግ ናፍቄ
አንጐራጉራለሁ አንጐራጉራለሁ (፪x)


የሚታየውንም ፡ ማይየውንም

በላይ ፡ ሠማይ ፡ ቢሆን ፡ ፦በታች ፡ በምድርም ፦(፪x)

ሁሉን በየስፍራው አስተካክሎ አኖረው

አቤት አቤት ሥራው ፦እግዚአብሔር ጌታ ነው ፦(፪x)


አዝ፦ቅኔን እቀኛለሁ ቅኔን እቀኛለሁ
የእጆቹን ሥራ እያየሁ
ትርጉም አለው ለእኔ
ይሄ ሁሉ የማየውን አሃሃሃ
በፊቱ ለማየት እጅግ ናፍቄ
አንጐራጉራለሁ አንጐራጉራለሁ (፪x)