ከሰማሁት ፡ በላይ (Kesemahut Belay) - ማሜ ፡ ወርቁ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ማሜ ፡ ወርቁ
(Mamay Worku)

Mamay Worku 1.jpg


(1)

ህልሜ
(Helmie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:28
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የማሜ ፡ ወርቁ ፡ አልበሞች
(Albums by Mamay Worku)

አምላክነትህን ፡ ታላቅነትህ ፡ ጌትነትህ
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ከገመትኩት
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ከገመትኩት (፪x)

አምላኬ (፫x) ፡ እያልኩኝ
በፊትህ ፡ ብሰግድ ፡ ያለኝን ፡ ባስቀምጥ
ቃላት ፡ አላገኝም ፡ ክብርህን ፡ የሚገልጥ (፪x)

አዝ፦ መልካምነትህ ፡ አባትነትህ ፡ ደግነትህ
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ከገመትኩት (፪x)

ምህረት ፡ ቸርነትህ ፡ ተከትለውኛል
በፀጋ ፡ ላይ ፡ ፀጋ ፡ ፍቅርህ ፡ ደግፎኛል
መልካም ፡ ነህ ፡ አምላኬ ፡ በስጦታህ ፡ አትጸጸት
ቆጥሬ ፡ አልጨርስም ፡ ጌታ ፡ የአንተን ፡ ደግነት (፪x)

አዝ፦ መልካምነትህ ፡ አባትነትህ ፡ ደግነትህ
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ከገመትኩት (፪x)

በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ የማውቀው ፡ እውነቱ
ቀዝቅዞ ፡ አያውቅም ፡ መውደድህ ፡ ግለቱ
የፍቅርህ ፡ ስፋቱ ፡ ልክ ፡ የለው ፡ ጥልቀቱ
በመስቀል ፡ ተገልጧል ፡ አምሳያ ፡ ማጣቱ

አዝ፦ አምላክነትህ ፡ ታማኝነትህ ፡ ወዳጅነትህ
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ከገመትኩት (፪x)