ዘንድሮማ (Zenderoma) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 3.jpg


(3)

የናርዶስ ፡ ሽቶዬ
(Yenardos Shetoyie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 7:32
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

የማልጠብቀው ፡ በህልሜም ፡ በውኔ
የሠራዊት ፡ ጌታ ፡ እንዳሳየኝ ፡ በዓይኔ (፪x)
ኧረ ፡ ይሄማ ፡ ሌላ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
ዘንድሮማ ፡ ሌላ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
ኧረ ፡ ይሄማ ፡ ሌላ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
መድኃኒቴ ፡ በሕይወቴ ፡ ለእኔ ፡ ያደረገው

መለኮታዊ ፡ ግርማ ፡ ሞገስ
ከአምላኬ ፡ ዙፋን ፡ ከላይ ፡ ሲፈስ (፪x)
አየሁ ፡ ሕይወቴን ፡ ሲያረሰርስ (፪x)
አየሁ ፡ ኑሮዬን ፡ ሲያረሰርስ (፪x)

የናፈኳቸው ፡ የሞተስ ፡ ምንጮጭ
ተከፍተውልኝ ፡ የሰማይ ፡ ደጆች
አየሁ ፡ ሲያጠግቡኝ ፡ የእግዚአብሔር ፡ እጆች (፪x)
አየሁ ፡ ሲያጠግቡኝ ፡ የእግዚአብሔር ፡ እጆች (፪x)

የማልጠብቀው ፡ በህልሜም ፡ በውኔ
የሠራዊት ፡ ጌታ ፡ እንዳሳየኝ ፡ በዓይኔ (፪x)
ኧረ ፡ ይሄማ ፡ ሌላ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
ዘንድሮማ ፡ ሌላ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
ኧረ ፡ ይሄማ ፡ ሌላ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
መድኃኒቴ ፡ በሕይወቴ ፡ ለእኔ ፡ ያደረገው

የትንቢቱ ፡ ቃል ፡ ሥጋን ፡ ለበሰ
የተወሰደው ፡ ምርኮ ፡ ተመለሰ (፪x)
ይኸው ፡ እንደ ፡ ንሥር ፡ ኃይሌ ፡ ታደሰ (፪x)
ይኸው ፡ እንደ ፡ ንሥር ፡ ኃይሌ ፡ ታደሰ (፪x)

የልምላሜ ፡ የመጐገብኘት
የሞገስና ፡ የመፅናናት
አንድ ፡ ነው ፡ ምንጩ ፡ የበረከት (፪x)
አንድ ፡ ነው ፡ ምንጩ ፡ የበረከት (፪x)

ፍቅርህ ፡ ይጣፍጣል (፫x)
ማራ ፡ የሆነውን ፡ መራራውን
ሕይወት ፡ ያጣፍጣል
ይጣፍጣል ፡ ይጣፍጣል
ፍቅርህ ፡ ይጣፍጣል (፪x)

ደስ ፡ ያለው ፡ ሰው ፡ በአምላኩ ፡ የኮራ
ምን ፡ ያደርጋል ፡ እስኪ ፡ ንገሩኛ
ደስ ፡ ያለው ፡ ሰው ፡ በኢየሱስ ፡ የኮራ
ምን ፡ ያደርጋል ፡ እስኪ ፡ ንገሩኛ
ማመልክ ፡ ነው ፡ እንጂ
ይህንን ፡ ድንቅ ፡ ጌታ (፬x)
ደስ ፡ ያለው ፡ ሰው ፡ በኢየሱስ ፡ የኮራ
ምን ፡ ያደርጋል ፡ እስኪ ፡ ንገሩኛ
ማመልክ ፡ ነው ፡ እንጂ
ይህንን ፡ ድንቅ ፡ ጌታ (፬x)

የማይገርም ፡ ካለ ፡ የእግዚአብሔርን ፡ ጥበብን ፡ አይቶ
አሃሃሃ ፡ አይቶ
ይህ ፡ ህመም ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ አይደለም ፡ ጤንነት ፡ ከቶ
አሃሃሃ ፡ ከቶ
አሥር ፡ ጊዜ ፡ አይኖር ፡ የሚኖረው ፡ አንዴ
አሃሃሃ ፡ አንዴ
ሰው ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ኖሮ ፡ ቢሞትስ ፡ ይቆጨዋል ፡ እንዴ
አሃሃሃ ፡ እንዴ

አሥር ፡ ጊዜ ፡ አይኖር ፡ የሚኖረው ፡ አንዴ
አሃሃሃ ፡ አንዴ
ለኢየሱሴ ፡ ኖሬ ፡ ብሞትስ ፡ ይቆጨኛል ፡ እንዴ
አሃሃሃ ፡ እንዴ (፪x)

ለውዴ ፡ አሃሃሃ ፡ ለውዴ (፪x)
ለውዴ ፡ ኦሆሆሆ ፡ ለውዴ
ለውዴ ፡ አሃሃሃ ፡ ለውዴ